ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው)

(ከኃይሉ ገብረዮሐንስ የተዛወረ)

ኃይሉ ገ/ዮሐንስ (ገሞራው) 1928 ዓ.ም ከአባቱ መርጌታ ገ/ዮሐንስ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ አካባቢ ተወልዶ በልጅነቱ የቤተክርስቲያን ትምህርት ቀስሟል። መደበኛ ትምህርቱን በምኒሊክ ት/ቤት እየተከታተለ በስላሴ ቤተክርስቲያን በድቁና ያገለግል የነበረው ገሞራው፤ በልጅነቱ የተካነበት የግእዝ ቋንቋ ከቀሳውስቱ ጋር እንደፈለገ በቅኔ እንዲግባባ አስችሎታል። ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ስር የሚገኘውን መንፈሳዊ ኮሌጅ ተቀላቀለ። ከመንፈሳዊ ትምህርት ይልቅ ፍልስፍና ቀልቡን ስለገዛው ወደ ኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናት ተቋም ተቀይሮ የሚወደውን ስነ ጽሁፍ ማጥናት ቀጠለ።

የደራሲና ባለቅኔው ስራዎች በጥቂቱ “አንድነት ግጥም” (እማማ አፍሪካን ለማስታወስ)፣ “በረከተ መርገም”፣ “የበሰለው ያራል”፣ “በናቴኮ ሴት ነኝ”፣ “እናትክን በሉልኝ”፣ “የሽግግር ደባ”፣ “ዛር ነው በሽታዋ”፣ “ቅኔ ለዘመን”፣ “ቆርጠሃት ታለለ”፣ “የመንጎል ጥሪ”፣ “ዜሮ ፊታውራሪ” ይሰኛሉ።[1]

አንድነት ግጥም (እማማ አፍሪካን ለማስታወስ) 1984 87 ገጽ
በረከተ መርገም 1987 ISBN 91-7328-627-3 96 ገጽ
የበሰለው ያራል 1988 ISBN 91-7328-638-9 224 ገጽ
በናቴኮ ሴት ነኝ 1989 243 ገጽ
እናትክን በሉልኝ 1989 ISBN 91-7328-774-1 134 ገጽ
የሽግግር ደባ (?) 1990 ISBN 91-7328-675-3 353 ገጽ
ዛር ነው በሽታዋ 1991 208 ገጽ
ቅኔ ለዘመን 1992 ገጽ274
ቆርጠሃት ታለለ (?) 1992 290 ገጽ
የመንጎል ጥሪ 1994 ISBN 91-630-2924-3 108 ገጽ ]]
ዜሮ ፊታውራሪ 1995 ISBN 91-7328-768-7 55 ገጽ ]]

ሌሎቸ ስራዎች ለማስተካከል

Mao Zedong, Weida de jinbu zhi fu! - Stockholm : F�rfattares bokmaskin : [Stockholm] : [G.Y. Hailu], 1986. - 38 s. : ill. - ISBN 91-7328-536-6

Hanying chengyu di xiaojia = A tiny home of Chinese-English idiomatic phrases / compiled by Hailu - [Stockholm] : [F�rfattares bokmaskin] : [Stockholm] : [G.Y. Hailu], 1987. - xxxix, [1], 478 s. - ISBN 91-7328-598-6
ምንጭ ስዊዲን አብያተ መጻሕፍት ዝርዝር

  1. ^ https://www.goodreads.com/author/show/1218955