«እናትክን!» በሉልኝ

ይፈሳል ይሉኛል፣ አባይ ዐይኑ ይፍሰስ

ያን ስንቱን ወገኔን የውሃ እጦት ሲያምስ

የድርቀት ጋንጩራ ሲበላ ስንቱን ነፍስ፣

ውሃ ውሃ እያለ ለጋው ሲቀነጠስ

ናይል አባያችን . አለ ነበር ሲፈስ

ለፈፀመው ደባ ለሰራውም ግፉ

«እናትክን!» በሉልኝ በዚያ የምታልፉ ገጣሚ እና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሀንስ (ገሞራው)