ባቢሎን በሳሎን

ከታህሳስ 17፣ 2002 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ተአትር ለዕይታ የበቃ የኮመዲ ዘውግ ያለው የውድነህ ክፍሌ ድርሰት

ባቢሎን በሳሎን ከታህሳስ 17፣ 2002 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ተአትር ለዕይታ የበቃ የኮመዲ ዘውግ ያለው የውድነህ ክፍሌ ድርሰት ሲሆን አዘጋጁ ደግሞ ተስፋዬ ገብረሐና ናቸው።[1] በሕዝቡ ጥያቄ መሠረት በድጋሚ ወደ መድረክ መጋቢት 18 ቀን 2011 ዓ.ም ተመልሶም ነበር። [2]

ጭብጡ ለማስተካከል

ውብሸት እና ትዝታ አብሮ መኖርም ሆነ መለያየት ያልሆነላቸው ባልና ሚስት ናቸው። አንዱ የሌላውን እልህ ለማስወጣት ተግቶ እንቅልፍ ያጣል። በግድግዳ በከፈሉት ሳሌናቸው ውስጥ ተፈላጊነታቸውን እና ተደማጭነታቸውን ለማወጅ የቅናት የእልህ ጦር ይመዛሉ።[1]

ተዋንያን ለማስተካከል

  • ለማየሁ ታደሰ
  • ሉሌ አሻጋሬ
  • እመቤት ወልደገብርኤል (ራሄል ተሾመ)
  • ህንፀተ ታደሰ
  • እንድሪስ አህመድ
  • ስናፍቅሽ ተስፋዬ
  • ፍቃዱ ከበደ
  • ዳንኤል ተገኝ

ዋቢ ለማስተካከል

  1. ^ "Ethiopian National Theatre" (በen).
  2. ^ "Ethiopian National Theatre" (በen).