ቀዓት (ዕብራይስጥ፦ /ቀሃት/፤ ግሪክኛ፦ /ካዓጥ/) በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት የሌዊ ልጅ፣ የእንበረም አባትና የሙሴ አያት ነበር።

ኦሪት ዘጸአት ፮፡፲፰ ዘንድ፣ የቀዓት ሌሎች ልጆች ይስዓርኬብሮን እና ዑዝኤል ተባሉ፤ የቀዓትም እድሜ 133 ዓመታት ደረሰ። በኦሪት ዘኊልቊ ምዕራፍ ፫ እና ፬ እንደሚለን፣ የቀዓት ትውልድ ወይም ቀዓታውያንሌዋውያን መካከል አንዱ ወገን ናቸው፤ የዚህም ወገን ኃላፊነት ታቦትና ቅዱስ ንዋይ ነው።

መጽሐፈ ኩፋሌ ፳፬፡፳፮ የሌዊ ሚስት ስም ሜልካ፣ «ከቃራ (ወይም በሌሎቹ ቅጂዎች ታራ) ልጆች ወገን ከሚሆን ከአራም ልጆች የተወለደች»፣ ይህችም የቀዓት እናት ነበረች። ኩፋሌ ፴፩፡፲፩ ቀዓት ከሌዊ ልጆች ጋር ወደ ግብፅ ከገቡት ሰዎች መካከል ይዘረዝራል።

በተጨማሪ «የሌዊ ምስክር» የተባለው ጽሑፍ (ከ፲፪ቱ አበው ምስክሮች አንዱ) እንዲህ ይላል፦

«እንግዲህ እኔ (ሌዊ) ሚስትን ሳገባ ዕድሜዬ 28 ዓመታት ነበር፣ ስምዋም ሜልካ ነበር።... ቀዓትም በኔ 35ኛው ዓመት፣ ወደ ምሥራቅ (ግብጽን ሳይገቡ)፣ ተወለደ። በራዕይም እሱ በጉባኤው ሁሉ መካከል ከፍ ብሎ እየቆመ አየሁ። ስለዚህ ስሙን «ቀዓት» አልኩት፣ «የግርማዊነትና የትምህርት መጀመርያ» ማለት ነው።»