መቅመቆ (Rumex abyssinicus) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

መቅመቆ

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ ለማስተካከል

አስተዳደግ ለማስተካከል

የእርሻም ሆነ የውድማ አረም ነው።

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር ለማስተካከል

የተክሉ ጥቅም ለማስተካከል

ድንቼው ቀይ ንክር ቀለም ይሠራል፣ የሴቶች እጅና እግር ለማጌጥ ነው። ድንቼው ሲበሠል ጠንካራ ቢጫ ንክር ቀለም ይሠራል፣ ይህም ለቅቤና ለቅመም ነው።[1]

በባሕል መድሃኒት፣ ሥሩ በቋቁቻ ላይ በቀጥታ ይቀባል። ሥሩም ተደቅቆ በውሃ ተፈልቶ ለደም ብዛት ለማከም ይጠጣል።[2] ሥሩም ለደም ብዛት ወይም ለጉሮሮ ብግነት ይኘካል። ሥሩ ተደቅቆ በወተትና ቅቤ ለእንቅርትና ለአሚባ በሽታ ይጠጣል።[3]

  1. ^ አማራ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ በደብረ ሊባኖስ ዙሪያ ያለው ሕዝብ መድሃኒታዊ እጾች እውቀናና ጥቅም 1998 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ ግርማይ መድኅን፣ ያለም መኮነን፣ አዲስ አበባ ዩኒቬርሲቴ፣ አክሊሉ ለማ ተቋም
  3. ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች