ከ«ሎዥባን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 1፦
'''ሎዥባን''' በ 1987 እ.ኤ.አ. የተፈጠረ [[ሰው ሠራሽ ቋንቋ]] ነው። ቋንቋው የተፈጠረ በLogical Languages Group (LLG, "ትክክለኛ አሰተሳሰብ ያለው ቋንቋ ስብሰባ") በሚባል የ[[ዋሺንግተን ዲሲ]] ተቋም ነው። LLG በ1955 እ.ኤ.አ. መጀመርያ የፈጠረ ቋንቋ "[[ሎግላን]]" ተባለ። ሎዥባን ከሎግላን ተሻሽሎ የወጣ ቋንቋ ይባላል።
አላማቸው ስዋሰው በሰዎችና በ[[ኮምፕዩተር]] በቀላል የሚታወቅ የ"ትክክለኛ አስተሣሠብ ቋንቋ" ለመፍጠር ነበር። ሌሎች ሰው ሰራሽ ቋንቋዎች ለምሳሌ [[ኤስፔራንቶ]] የተፈጠሩ በተለይ ከ[[አውሮጳ]] ቋንቋዎች ቃላት በመልቀም ነበር። ሎዥባን ግን "ባሕላዊ ገለልተኝነት" ለማሳየት እየሞከረ ነው። ነገር ግን
ቃላቱ የተፈጠሩ ብዙ ተናጋሪዎች ያላቸው 6ቱ የሰው ልጅ ቋንቋዎች በማነጻጸር ነበር። እነዚህም ቋንቋዎች [[ቻይንኛ]]፣ [[ህንዲ]]/[[ዑርዱ]]፣ [[እንግሊዝኛ]]፣ [[እስፓንኛ]]፣ [[ዐረብኛ]]ና [[መስኮብኛ]] ናቸው። ለያንዳንዱ ቃል ስንት ድምጾች አንድላይ ከነዚህ ቋንቋዎች ጋራ እንዳለው በኮምፒዩተር ተቆጠረ። ስለዚህ
*prenu (ፕረኑ) = ሰው
*cukta (ሹክታ) = መጽሐፍ
*vanju (ቫንዡ) = የወይን ጠጅ
እነዚህ በኮምፒዩተር የተፈጠሩ ቃላት እንደ ሌላ ቋንቋ ባይመስሉም፣ ክፍሎች ግን ከትልቁ ቋንቋዎች መታየታቸው ይቻላል። ለምሳሌ በ"ፕረኑ" የእንግሊዝኛ "ፐር-" (per-) ከ"ፐርሶን" (person)፣ እና የቻይንና "ረን" (人) ይታያሉ። "ሹክታ" ደግሞ የእንግሊዝኛ "-ኡክ" ከ"ቡክ" (book)፣ የቻይንኛ "ሹ" (书)፣ እና የዐረብኛ "ኪታብ" ( كتاب ) ያዋሕዳል። "ቫንዡ" የ[[ፈረንሳይኛ]] "ቫን" (vin) እና የቻይንኛ ጅዮ (酒) ይመስላል።
የሎዥባን [[ስዋሰው]] እንደ ኮምፕዩተር ቋንቋ ይመስላል።
==ምሳሌ ዐረፍተ ነገሮች==
|