ከ«ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
add some links for now, probably needs more links eventually |
||
መስመር፡ 1፦
[[Image:Kidane Aba Kesto.jpg|thumb|300px]]
'''ኪዳኔ ወልደመድኅን''' ዓርብ [[ሐምሌ 2]] ቀን [[1907]] ዓ.ም [[ቡልጋ]]
አካለ መጠን ሲደርሱ በ18 ዓመታቸው
በዚህ ጦር [[ግንባር 9]] ወራት ለበሽሊንዲ፤ [[ዋቢ
ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ከተቀላቀሉ በኋላም በደንዲ፤ በሶዶ፤ በበዳቄሮ እና በመሳስሉ ሥፍራዎች አርበኝነታቸውን እስከ ጥቅምት [[1931]] ዓ.ም ድረስ ሲያካሂዱ ከቆዮ በኋላ በዳቄሮ ከሚባለው ሥፍራ ላይ ከ [[ዱካ
ባሻ ኪዳኔ ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ከሙሴ ቀስተኛ የተማረከውን አላስረክብም በማለታቸውና በሌላም ምክንያቶች ባለመስማማታቸው፤ በኅዳር ወር 1931 ዓ.ም. አባሎቻቸውን አስከትለው ወደ ትውልድ አገራቸው ወደቡልጋ ተጉዘው በ12 ቀናቸውም ቡልጋ ገቡ። እዚሁም ከፊታውራሪ ኃይለማሪያም ማናህሌ እና ከፊታውራሪ ተረፈ ማናህሌ ጋር ተቀላቅለው እስከ መጋቢት 1931 ዓ.ም. ድረስ በውሽንግር፤ ጨፌ ዶንሳ ምሽግ፤ ነጭ ድንጋይ ምሽግ፤ ልዝብ ድንጋይ ከተባሉ ቦታዎች ላይ ከጠላት ኃይል ጋር ሲዋጉ ከርመው በመጋቢት ወር በሃገሩ ላይ ገብቶ በነበረው የእንቅጥቅጥ በሽታ በጽኑ ታመው ከልዝብ ድንጋይ ምሽግና ቤቶች ነጭ ድንጋይ ጦስኝ ምሽግ ከወደምስራቅ ኮረማሽ መካከል ታመው ተኙ:: ወዲያው በሰኔ ወር ሦሥት አምባ ላይ ሰፍረው ሳሉ ጠላት በሦስት አምባ፤ በወይን አምባ እና በጦስኝ በኩል ወርዶ ሲከባቸው ባሻ ኪዳኔ ገመምተኛ ስለነበሩ መሮጥ አቅቷቸው ‘ተማረክ’ እያለ የከበባቸውን የጠላት ጦር እየተከላለከሉ ጫካ ገቡ የጠላትም ወታደሮች የገቡባት ጠፍቶባቸው ሲፈልጉ ባሻ ኪዳኔ ጎርፍ በጀለጣት ዛፍ ተንጠልጥለው ደፍጠው ሲጠባበቁ ጠላት ጫካውን በእሳት ነበልባል ግራና ቀኙን ሲያቃጥልው እሳቸው ያሉባት ሳትቃጠል ሊተርፉ ቻሉ። ከሦስት ቀንም በኋላ ጠላት ለቆ ሲሄድ ባሻ ኪዳኔ ከጅረት ወርደው ውሃ ሲጠጡ ደክመው ወድቀው ሳሉ ወንድማቸውና ሌሎች ሲፈልጓቸው በጥይት ያሉበትን አሳወቋቸውና መጥተው በቃሬዛ አዛውሯቸው፡
ከዚህ በኋላ ክረምቱን ቡልጋ ውስጥ በነጭ ድንጋይ፤ፍልፍል አፈር፤ ጦስኝ ምሽግ፤ በመስኖ ከነደጃዝማች ሀብተ ሥላሴ፤ ከነፊታውራሪ በለጠ ሳሴና ፊታውራሪ አጎናፍር ሌሎችም ስመጥሩ የቡልጋ ልጆች ጋር ሆነው ጠላትን ሲያጠቁና ሲከላከሉ ቆይተው በመስከረም [[1932]] ዓ.ም በሰገሌ በኩል ተጉዘው ጊሊላ ላይ ከራስ አበበ አረጋይ ጋር ሲቀላቀሉ ባሻ ኪዳኔ የግራአዝማችነት ማእረግ ተሾሙ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ
===የሰሜን ዘመቻ===
ቀኛዝማች ኪዳኔ በ1933 ዓ.ም ዳውንት፤ ተንታ፤ ደብረታቦር ላይ የሰፈረውን የጣሊያን ወታደሮች ከጓደኞቻቸው ጋር እየማረኩ በመስከረም [[1934]] ዓ.ም ጉማራ ላይ ከፍ ያለ ውጊያ አድርገው ጠላትን ድል አደረጉ።
[[ኅዳር 12]] ቀን 1934 ዓ.ም ከጎንደር ወደ ቁልቋል በር ላለው የጠላት ጦር ስንቅ ሊያቀብል ከባድ መኪና፤ ታንክና መድፍ ጭኖ የመጣውን ኃይል ገጥመውት አሸንፏቸው ስንቁን አቀብሎ ሲመለስ እንደገና አጥቅተው ብዙ ባንዳዎች ገደሉ።
[[ኅዳር 18]] ቀን 1934 ዓ.ም ጎንደር ከተማ ውስጥ ጄነራል ናሲ ከብዙ ሺህ ሰራዊት ጋር አካባቢውን በሽቦ አጥሮ በሽቦው ውስጥና ውጭ ፈንጂ ቦንብ ከምሱሩን ነቅሎ ቀብሮበት ሳለ፡ በእንግሊዙ ማጆር ዳግላስ መሪነት ቀኛዝማች ኪዳኔ ይኼንኑ የተቀበረ ቦንብ በመቀስ እየቆረጡ ለሊቱን ተጉዘው ምሽጉ ሲደርሱ ከበው ሲነጋ ተኩስ ተከፈተ። ጠላትም ከከፍተኛ ተራራ ላይ ወደታች ወደነ ቀኛዝማች ኪዳኔ በቦንባርድና ከባድ መትረየስ ሲያጠቃቸው በተራራው ሥር ሥር አድገው ወደ ጎንደር ከተማ የሚወስደውን መንገድ ላይ ሲደርሱ ከጎንደር ከተማ የሚመጡ አስመስለው ከኋላው በጨበጣ የጅ ቦንብ እየጣሉ ብዙ ወታደሮች ፈጁ። እንዲሁም ሦስት ቦንባርድና ስድስት የውሐ መትረየስ ማርከው ምሽጉን አስለቅቀው ከያዙ በኋላ ጀነራል ናሲ ወዳለበት ወደጎንደር ቀጠሉ። ጎንደርም ሲገቡ በአሶ ቤተክርስቲያን ምሽግ በኩል ፋሲል ግንብ ምሽግ ሲደርሱ ምሽጉን ለመድፈር የጅ ቦንብ ምሽጉ ላይ በብዛት ሲጥሉ ጠላት ተሸንፎ የሰላም ባንዲራ አውጣ። በዚህ ጊዜ ቀኛዝማች የጠላትን ወታደሮች ለመማረክ ሲጠጉ የነቀሉትን የጅ ቦንብ ለስተው ኪሳቸው ከተቱ። ወዲያው 480 ነጮች በጃቸው ተማርከው በከተማው የሚገኙትን የአረብ ተወላጆች ሱቅና ገንዘብ እንዳይዘረፍ በወታደር አስጠብቀው ከምሽቱ ሁለት ሰዐት ላይ ተማራኪዎቹን ለ ማጆር ዳግላስ አስረክበው እረፍት ሲያደርጉ ቀን በ ዘጠኝ ሰዐት ገደማ የነቀሉት ቦንብ ከምሽቱ ሁለት ሰዐት ላይ ከኪሳቸው ላስቲኩ ተነቅሎ ሳይፈነዳ ተወርውሮ ሲጣል ፈነዳ።
የጎንደርም ጦርነት [[ኅዳር 19]] ቀን 1934 ዓ.ም ተፈጽሞ ባራት ቀኑ አልጋወራሹ መጥተው ወዲያው ከሳቸው ጋር
[[የካቲት 18]] ቀን 1934 ዓ.ም የፊታውራሪነት ማእረግ ተሰጥተው መጀመሪአ በ ወረዳ አስተዳዳሪነት ከዚያም
ከፋ ውስጥ እንደተሾሙ (1943 ዓ.ም) ከጠቅላይ ገዢው ጋር ባለመስማማታቸው ተሽረው ንጉሠ ነገሥቱ ከስልጣን እስከወረዱ ድረስ በእስራትና በግዞት 23 ዓመት ሙሉ ለሃገሩ እንዳልተጋደ፣ በአርበኝነት ደሙን እንዳላፈሰሰ፣ ለኢትዮጵያ ነጻነት መስዋዕት እንዳልሆነ ተቆጥረው፣ ንጉሠ ነገሥቱ ለቅርብ ሎሌአቸው አድልተው ደጃዝማች ኪዳኔን ከሀገር አገልግሎት አስወገዷቸው።
ንጉሠ ነገሥቱ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ደጃዝማች ኪዳኔ በመላ ኢትዮጵያ አርበኞች በሊቀመንበርነት ተመርጠው ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ [[ጥቅምት 9]] ቀን [[1971]] ዓ.ም በተወለዱ በ65 ዓመታቸው አረፉ።
[[Image:Dejazmachkidane.jpg|thumb|300px]]
[[Category:የኢትዮጵያ ሰዎች]]
|