ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
መስመር፡ 317፦
፱. ኣራት ነጥብ (“።”) እራሱን የቻለ ኣንድ የግዕዝ የምልክት ቀለም ነው። ኣንዳንድ ደራስያን ምልክቱን ከሁለት ባለሁለት ነጥቦች (ነቊጦች) ወይንም በእንግሊዝኛ ኮለን (“Colon”) መክተብ ስለጀመሩ ይህ ትክክል ከኣለመሆኑም ሌላ ኣስፈላጊ ያልሆኑ ሁለት መርገጫዎች በማስጨመር ጊዜና ስፍራ የሚያስባክን ግድፈት ነው። ከሁለት ቀለሞች የተሠሩትን ለመሠረዝም ሁለት መሠረዣዎች ያስፈልጋሉ። ኣራት ነጥቦች የሌሉት ጽሑፍም ችግር ውስጥ ሊወድቅ ይችላል። ፲. ዶክተሩ የእንግሊዝኛው ኮለን ለግዕዝ እንዲጠቅም ያደረጉት በኮለንነት ስለሆነ የግሉ የዩኒኮድ ቊጥር ከኣለው ባለሁለት ነጥብ (ወይም ነቊጥ) የባዶ ስፍራ የግዕዝ ምልክታችን ጋርም ኣንድ ኣይደለም። ኣራት ነጥብን ከሁለት ባለ ሁለት ነጥቦች (“፡”) በኮምፕዩተር መክተብም ግድፈት ነው። ምክንያቱም ይህ ኣሠራር ኣራት ነጥቦች ከሌሉት የኣማርኛ የታይፕ መጻፊያ የመጣ የኣሠራር ችግር ስለሆነ [http://web.archive.org/web/20120107191057/http://www.ethiopic.com/Rabies_in_Amharic.pdf] እንጂ ሁለት ባለ ሁለት ነጥቦች ኣራት ነጥቦች የሚሆኑበት ኣከታተብ ወደ ኮምፕዩተር እንዳይገባ ዶክተሩ ከተከላከሉት ኣንዱ የጎደለ ኣጠቃቀም ነው። [http://sirius-c.ncat.edu/eas/news/EJSciTech/abera2.html] በሞዴት፣ ኢትዮወርድ፣ ግዕዝኤዲት በኮምፕዩተርና ግዕዝኤዲት በእጅ ስልክ የግዕዝ ኣራት ነጥብ ምልክት የተከተበውና እየተከተበ የኣለው በሁለት መርገጫዎች (“ዝቅ 3”) ነው። በግዕዝ ዩኒኮድ መደብ ውስጥ እንደሚታየው [http://unicode.org/charts/PDF/U1200.pdf] እና እዚህ ጎን ላይ የኣለው ሥዕል እንደሚያሳየው ሁለት ነጥብና ኣራት ነጥብ የተለያዩ ናቸው። ሁለት ሁለት ነጥብና ኣራት ነጥብ የተለያዩ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ኣራት ነጥብን በማያስከትብ ፕሮግራም መጠቀም የለባቸውም። ፲፩. የመጽሓፎች ይዘት (Contents) እና ማውጫ (Index) የተለያዩ ናቸው። ፲፪. የኣንዳንዶች ስሕተቶች ምንጮች የተሳሳቱ ፊደላት ወይም መክተቢያዎች ናቸው፦ ምሳሌ “ቍጥር”ን በ“ቁጥር” መጻፍ።
፲፫. “ው”ን አንጂ “ዉ”ን የሚጠቀሙ ብዙ የዓማርኛ ቃላት የሉም። በቅርቡ ግን በኣለማወቅ በ“ው” ቀለም ምትክ “ዉ”ን በግድፈት የሚጠቀሙ ፀሓፊዎች እየበዙ ነውና ቢታሰብበት ኣይከፋም። [[መዝገበ ቃላት]]ም ጠቃሚዎች ናቸው። ([[እንግሊዝኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት 1972]])። “ው”ን በትክክል ከ40 በላይ ቃላት ውስጥ የተጠቀመ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [http://www.dejeselam.org/2014/03/blog-post_29.html] “ው”ን በስሕተት ከ400 በላይ ቃላት ውስጥ የተጠቀመ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [https://hornaffairs.com/am/2017/01/24/committed-leadership-corruption/] ፲፬. የግዕዙ “ሀ” ድምጽ ወደ “ኸ” የቀረበ ነው። “አ” እና “ኣ” ድምጽ ኣይጋሩም። [http://www.ethiopic.com/amharic/errors.pdf] [http://web.archive.org/web/20030315142841/] [http://web.archive.org/web/20120111013212/http://www.ethiopic.com/ethiopic_alphabet.htm] [http://dagmawibelete.blogspot.com/2013/05/ethiopic.html] ፲፭. ኣንዳንድ ፀሓፊዎች በነጠላ ሰረዝ (“፣”) ምትክ ኮማ (“,”) (Comma) በኣራት ነጥብ (“።”) ምትክ ፔርየድ (“.”) (Period) መጠቀም ስለጀመሩ ፊደሉንና ቋንቋውን እያበላሿቸው ናቸው። ፲፭. ኣንዳንድ ምሁራን ስለማያስተውሉ ሁሉንም የዓማርኛ ቃላት መክተብ በማይችሉ እየተጠቀሙ የሚያወሩትን መጻፍ ኣይችሉም። የግዕዝ ፊደል ታዋቂነት የኣለ እስፔሊንግ ስሕተት ድምጽን በማስፈር ትክክክለኛ ድምፃዊ ፊደል መሆኑ ነው። ፲፮. ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በሦስት መርገጫዎች መክተብ ጊዜና ጉልበት ማባከን ነው። (Typing any Ethiopic glyph with three keystrokes is a waste of time and effort.) ምክንያቱም የዶክተሩ ኣሠራር እንግሊዝኛውን ከኣጋጠመው ችግር ጭምር ለማላቀቅ እንጂ ለግዕዙ የእንግሊዝኛውን ችግር
፳፩. የግዕዝ ፊደል የኦሮምኛው ፊደል ውስጥ ያለውን የግዕዙን “ዸ” እና ሰባት እንዚራን ቀለሞቹን ያጠቃልላል። ስለዚህ እንደ “በዻዻ” የኣሉትን ቃላት በ“በዳዳ” ወይም “ዻራርቱ"ን በ“ደራርቱ” መክተብ ግድፈት ነው። የኦሮምኛው ፊደል የዶክተሩ ሞዴት፣ ኢትዮወርድ፣ ግዕዝኤዲትና ሌሎች ፕሮግራሞች ውስጥ ቀርበው የሚፈልጓቸው ተጠቅመውባቸዋል። ፳፪. ሁሉንም ቀለማት የሌሉት ወይም የማይከትቡ ዓማርኛ እየተባሉ ሲቀርቡ ኣለተቃውሞ መቀበል ነውር ነው። ምክንያቱም ይህ ለፊደሉና ለሰዋሰው የኣለመጨነቅን ስለሚያሳይ የፀሓፊዎችን ችሎታ
፳፭. ኣንዳንድ ሰዎች ዓማርኛ የእራሱ ፊደል የለውም ይላሉ። ዓማርኛ የእራሱ ፊደል (Amharic Alphabet) የኣለው ቋንቋ ነው። [https://en.wikipedia.org/wiki/Ge%27ez_script] የግዕዝም ቋንቋ የእራሱ ፊደል ኣለው። የግዕዝ ቋንቋ ፊደላት የዓማርኛው ውስጥ ሲኖሩ ሁሉም የዓማርኛ ፊደላት የግዕዙ ቋንቋ ፊደላት ውስጥ የሉም። ግዕዝ (Ge'ez) ወይም Ethiopic የተለያዩ ቋንቋዎች የሚጠቀሙበት የፊደሉም ስም ሲሆን ለተለያዩ ቋንቋዎች ተጨማሪ ቀለሞች ተጨምረዋል። ፳፮. የኣማርኛ የታይፕራይተር ፊደል የግዕዝ ፊደል ኣይደለም። የእውሸት (Fake) ወይም የፈጠራ የዓማርኛ ፊደል እንጂ የዓማርኛም ፊደል ኣይደለም። መጽሓፍትም ሲታተሙ የነበሩት በግዕዝ ፊደል በማተሚያ ቤቶች ትክክለኛ ቀለሞች ነበር። መጽሓፍት በብራናም ይሁን ሕዝቡ በእጁ ሲጽፍ የነበረው በግዕዝ ፊደል እንጂ በኣማርኛ ታይፕራይተር ፊደል ኣልነበረም። ኣሁንም ቢሆን በድሮው ዓይነት ወይም ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ በኣደረጉት መነሻው ይህ ፊደል በሆነው የዩኒኮድ የግዕዝ ፊደል ዓይነት ነው። [http://unicode.org/charts/PDF/U1200.pdf] የታይፕራይተርንና የማተሚያውን ፊደላት የማይለዩና ሁለቱ ኣንድ የሚመስሏቸው ኣሉ። ፳፰. በወልጋዳ፣ የተሳሳቱና ከሲታ ቀለማት ተጽፈው የሚቀርቡ ጽሑፎችና መጻሕፍት እየበዙ ነው። የፊደል መልክ ከኣላማረ ለማንበብም ኣያጓጓም። ጥሩ የግዕዝ ፊደል ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት “ነጋሪት ጋዜጣ”ን ሲያትምበት የነበረው ፊደል ነው። ብዙ መጻሕፍትም ታትመውበታል። [https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%98%E1%8B%B0%E1%89%A5:%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB_%E1%8C%B8%E1%88%93%E1%8D%8A%E1%8B%8E%E1%89%BD]
መስመር፡ 327፦
፴፫. ትክክለኛ ሰዋስው፣ የተሟሉ ቀለሞች፣ ትክክለኛ ቅርጾች እና የመሳሰሉትን በኣሌላቸው መጠቀም ለቋንቋው መዳከም ምክንያቶች እንዳይሆኑ መጠንቀቅ ኣስፈላጊዎች ናቸው። ስሕተቶች ሲደጋገሙ ሊለመዱ ይችላል። [https://www.facebook.com/getatchew.haile?hc_ref=ARRFkxIO467tAUBLSXTt7knkXxVL2anC-a6g_DTbwgxos8h3IbXzLdfI1m-Pb68lCJ8&fref=nf] ዶክተሩ ከሰዋስው ተሳሳቶች ኣንዱ ናቸው። ፴፬. ስለ ግዕዝና ዓማርኛ ፊደላት ሲጻፍ ስለ ግዕዝ ቋንቋ የሚመስሏቸው ኣሉና ይታሰብበት። ፴፭. ፊደላችን ለኣፍሪቃውያንና ሌሎችም እንዲተርፍ በወጉ መጠቀምና መንከባከብ ይጠቅማል። [https://ethiopianreporter.com/content/%E1%8B%A8%E1%8C%8D%E1%8B%95%E1%8B%9D-%E1%89%81%E1%8C%AD%E1%89%B5/] ፴፮. "ዓማርኛ" በግዕዙ "ዐ" የማይጻ'ፈው ቀለሙ ድምጹን ስለማይወክል ነው።
፴፯. ብዙ ስሕተቶችና ግድፈቶች የኣሉትን ጽሑፍ በዋቢነት ለመጠቀም ኣያስተማምንም። ምክንያቱም ደራሲው ኣስፈላጊዎቹን ጥንቃቄዎች ኣለማድረጉን ስለሚያሳይ ኣለመግዛት ወይም መተቸት ሳይሻል ኣይቀርም። ለምሳሌ ያህል "ነው" እና "ነህ" የመሳሰሉትን ቃላት "ነዉ" እና "ነክ" የሚሉ ኣሉ። "ኢትዮጵያ"ን በትክክል መጻፍ የማይችሉ ፊደል በሚገባ ኣልቈጠሩም ወይም ረስተዋል ማለት ኣይደለምን? ፴፰. የኣንድኣንዶቹ ስሕተቶች ምንጮች ኣዳዲሶቹ ማተሚያ ቤቶች ናቸው። ለምሳሌ ያህል ቀደም የኣሉ ጽሑፎች ውስጥ የ"ፏ" ፊደል መስመሩ የኣለው ከላይ ሆኖ ሳለ የኣዳዲሶቹ ከታች ነው። ቀደም የኣለውን ምልክት ዶክተሩ ሲጠቀሙ የተሳሳቱ የሚመስሏቸው ኣሉ። ይኸንኑ መቀጠያ ከግዕዝ ወግ ውጪ "ፍ" ላይ ተደርጎ በቅርቡ የቀረበ ፊደልም ኣለ። ማተሚያ ቤቶች በትክክለኛዎቹ ቀለሞች ከመቶ ዓመታት በላይ የተጠቀሙ ስለሆኑ መሪዎች እንጂ ተከታይ መሆን የለባቸውም። ፴፰. ዓማርኛ
===ሞክሼ ኆኄያት===
|