ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 456፦
፬. ኢ/ር ኣያና ብሩና ኢ/ር ተረፈ ራስወርቅ የዓማርኛውን ፊደላት በመቀነስና ቆርጦ በመቀጠል ኣማርኛ በመሰሉ የፈጠራ ቅርጾች የኣቀረቧቸው ሥራ ላይ ውለዋል። እነዚህ ቍርጥራጮች ግን የዓማርኛ ፊደሎች ኣይደሉም። ለእነዚህ ከመቶ በኣነሱ መቀጣጠያዎች የሚሠሩ የፈጠራ የኣማርኛ ነገሮች የሚያስፈልጋቸው ኣንድ የእንግሊዝኛ የፊደል ገበታ ስለሆነ በኣንዱ ገበታ ምትክ ብቻ የቀረቡ ናቸው። የዓማርኛ ቀለሞች ብዛት ከ200 በላይ ስለሆነ 100 ስፍራዎች ኣይበቁትም።
 
፭. ሆኄያቸውንኆኄያቸውን የጠበቁ የግዕዝና ዓማርኛ ጽሑፎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ለብዙ ዘመናት ተጽፈዋል። ፮. በእጅ ጽሑፍም ወረቀት ላይ መክተብ ለኢትዮጵያ ሕዝብና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ጠቅሟል። [https://henokspad.wordpress.com/2012/09/30/ሞክሼ-የአማርኛ-ፊደላት-እና-የባለሙያዎች/] ፯. ፊደል መቀነስ ትኩረት የኣገኘው “ፍቅር እስከ መቃብር” መጽሓፍ በተቀነሱ ፊደላት በ፲፱፻፶፪ ዓ.ም. ከታተመ በኋላ ነበር። እዚህ ላይ ተደርቦ ለታይፕራይተር ቴክኖሎጂ እንዲመች የፊደል ቅነሳ ክርክር ተጀምሮ በመጨረሻው ውድቅ ሆነ። ፰. የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መርሐ ልሳን [ኣካዴሚ] በ1973 ዓ.ም. ካወጣው የአጻጻፍ ሥርዓት ውሳኔ በስተቀር ሌላ ወሳኝ ጥናት ባለመደረጉ፣ ለዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ሊሆን የሚችሉ መምህራንንም ስለዚህ ጉዳይ ሆን ብሎ ያስተማራቸው ሰው ባለመኖሩ እነሱ ራሳቸው በዘፈቀደ ስለሚጽፉ ተማሪዎቻቸውም የነሱን ፈለግ በመከተል በዘፈቀደ ይጽፋሉ፤ የሚሉት ዶ/ር አምሳሉ አክሊሉ "የአማርኛን ሞክሼን ሆሄያት ጠንቅቆ ያለመጻፍ ችግርና መፍትሔ" የሚባል መጽሓፍም ጽፈዋል። ሃሌታው “ሀ”፣ ሓመሩ “ሐ”፣ ብዙኃኑ “ኀ”፣ ንጉሡ “ሠ”፣ እሳቱ “ሰ”፣ ኣልፋው “አ”፣ “ዓይኑ” “ዐ”፣ ጸሎቱ “ጸ”፣ ፀሐዩ “ፀ” የተባሉትን በማጥበቅና በማላላት ብቻ ለመግለጽ ኣስቸጋሪ ነው።
 
እንደ ዶ/ር ኣምሳሉ ተፈራ ኣገላለጽ "ከፊደላት ጋር የሚከሰቱ ችግሮችን ኣስመልክቶም በዓማርኛ ፊደል ገበታ ላይ ተመሳሳይ ድምጽ ያላቸው ስለሚገኙ፤ በኣጻጻፍ ረገድ በርካታ ልዩነቶች መኖራቸው፤ ራብዕ ድምፅ ያላቸው ከግዕዙ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ፊደላት መኖራቸው፤ ሳድስና ሳልስን እያቀያየሩ መጠቀም፣ ዲቃላዎችንና ፍንጽቅ ፈደላትን በዝርዝር የመጠቀም ዝንባሌ፣ በመሠረታዊ ቃሉ ላይ የሌለውን ቃል መጨመር፣ የኣናባቢዎች ቅጥል ኣለመለየት ችግሩን ይበልጥ እንዳሰፋው ጠቁመዋል። [https://eotcmk.org/a/%e1%88%80%e1%8c%88%e1%88%ad-%e1%8b%93%e1%89%80%e1%8d%8d-%e1%8b%90%e1%8b%8d%e1%8b%b0-%e1%8c%a5%e1%8a%93%e1%89%b5-%e1%89%b0%e1%8a%ab%e1%88%94%e1%8b%b0/]
(የእነዚህም ምሳሌዎች በቅደም ተከተል “ሀ" እና “ኀ"፤ “ሃገር" እና “ኣገር"፣ “አ" እና “ኣ"፣ “ግዜ" እና “ጊዜ"፣ “ፏፏቴን"ን በ“ፍዋፍዋቴ"፣ “ኈ"ን በ“ሆ"፣ “መምህራንን" በ“መምህራኖች" እና “ዮ"ን በ“ዬ" ዓይነቶች ናቸው በማለት በኣጠቃላይ ግን ችግሩ ከፊደሉ ሳይሆን ከተጠቃሚው ነው ይላሉ ዶ/ር ኣበራ።) ይህ ችግር በምሁራን ዘንድ ሞክሼ ቃላት ይቀነሱ፤ አይቀነሱ የሚለው ሐሳብ ዛሬም ድረስ እያከራከረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኣማራጮችንም በተመለከተ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ኣካዳሚ በ1973 ዓ.ም. ተመሳሳይ ድምፅ ያላቸው ፊደሎች ከገበታው ላይ ተቀንሰው በኣንድ ፊደል ብቻ ይወከሉ የሚል ሲሆን፣ የቤተ ክሕነት ሊቃውንት ኣቋም ደግሞ ፊደላት የፈጣሪን ቸርነት የሚገልጹ እና ከእሱ የተገኙ ስለሆኑ ሁሉም ጠንቅቆ ሊጽፋቸው ይገባል እንጂ በፍጹም ሊቀነሱ አይገባም።አይገባም ነው። ፊደላቱ በሙሉ መንፈሳዊ፣ ተፈጥሯዊና ሙያዊ ትርጓሜ ስላላቸው ያንን ያጣሉ በማለት" ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ይገልጻሉ። የኣብነት (ቄስ) ትምህርት ቤቶች ትኩርት መነፈግንም የሚጠቅሱ ኣሉ። [https://www.press.et/Ama/?p=1010]
 
፱. ከ1980 ዓ.ም. ወዲህም እነዚሁ ቀለሞች በዶ/ር ኣበራ ወደ ኮምፕዩተር ስለገቡ የግዕዝ ፊደላችንን የኣጋጠመው ችግር የለም። ይህ በእንዲህ እንዳለ የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በተቀነሱና በተቀነጠሱ ፊደላት “ኣማርኛ መዝገበ ቃላት” በ፲፱፻፺፫ ዓ.ም. እንዲሁም “ክብረ ነገስት ግእዝና ኣማርኛ” መጽሓፍት በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. ኣትሟል። በመጽሓፎቹ ርዕሶች “ኣማርኛ”፣ “ነገስት”ና “ግእዝ” ተብለው የቀረቡት “ዓ”፣ “ሥ” እና “ዕ” ከተቀነሱት ቀለሞቻቸው ውስጥ የተካተቱ በመሆናቸው ነው። እነዚህ ቍርጥራጮች ግን የዓማርኛ ፊደሎች ኣይደሉም። ክርክሩ በኣይቀነስ ባዮች ምክንያታዊ ኣሸናፊነት ማለቅ ሲገባው እንደቀጠለ ኣለ።
[https://afroaddis.wordpress.com/2011/04/03/ስለፊደል-ቅነሳ-የተደረጉ-ጥናቶች-ኢት/] [https://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=15385:አማርኛ-የራሱ-ፊደል-አለውን?&Itemid=211]
[https://www.facebook.com/888560754583711/posts/1364393447000437/] [http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=15565:የግዕዝ-ፊደልና-ቋንቋችን-የማንነት-ታሪካዊ-ቅርሳችን&Itemid=209]
[https://www.satenaw.com/amharic/wp-content/uploads/2017/11/facts-about-geez.pdf] [http://gothenburggebriel.com/2015/09/21/ሞክሼ-ፊደላት/] [http://www.goolgule.com/what-scholars-say-about-our-alphabet/] [https://www.youtube.com/watch?v=7sz8WBErBio] ይህ ሁሉ ሲደረግ የዩኒኮድ ዓማርኛ ቀለሞች ኣልተቀነሱም። ፲. ለብዙ መቶ ዓመታት በውጭ ኣገራትና ኢትዮጵያ ውስጥ በግዕዝ ፊደላችን ሲጠቀሙ የነበሩ ማተሚያ ቤቶች ፊደል ሲቀንሱ ኣልሰማንም።
፲፩.. ይህ የተዛባ የቅነሳ ኣጠቃቀም የመንግሥትም ፍላጎት ይመስላል። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዓይነት ተቋማት ፊደል መቀጠሉን ተዉት እንጂ በመቀነሱ ስለቀጠሉበት ነው። የግዕዝ ፊደል ትክክለኛ ኣጠቃቀም እያለ በተቀነሱና በተቈራረጡ ነገሮች መጠቀም መቀጠል በኮምፕዩተር ዘመን የሚያስከትለው ኪሳራ ቀላል ኣይደለም። ለምሳሌ ያህል በታይፕራይተር ዘመንና ይኸንኑ መሣሪያ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት ኣራት ነጥብን ሲከትቡ የነበሩት ሁለት ባለ ሁለት ነጥቦችን በመጠቀም ነበር። ዶ/ር ኣበራ ግን ለኣራት ነጥብ ከመነሻውም ኣንድ ስፍራ ስለመደቡለት ከዩኒኮድ በፊትም ይሁን በኋላ ፊደሉ የእራሱ የኮምፕዩተር ቍጥር ወይም ኮድ ኣለው። [https://www.youtube.com/watch?v=9m06K_NDqlo] ጥቂት ኣዳዲስ ፊደል ቀናሾች ወይም የግዕዝ መክተቢያ ኣቅራቢዎች ኣራት ነጥብን ከሁለት ባለ ሁለት ቀለሞች ማስከተብ ስለጀመሩ ጽሑፎቹ ኣራት ነጥብ የላቸውም። በኣሁኑ ጊዜ በብዙ ሚሊዮን የሚቈጠሩ ኢንተርኔት ላይ የኣሉ ኣራት ነጥብ የሌላቸው ጽሑፎች ማለቂያ የሌላቸው ናቸው። (የማለቂያን ቅኔነት የሚገባቸው ያውቁታል።) እነዚህን ስሕተቶች እየተከታተሉ ማረም ኣስቸጋሪ ስለሆነ ስሕተቶቹ እንዳይቀጥሉ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል። ሁለት ነጥቦች መካክል ተገብቶ ሁለቱን ብቻ በኣንድ መርገጫ መሰረዝ ከተቻለ መክተቢያውን ሆነ ፊደሉን ኣለመጠቀም ያዋጣል። ኣራት ነጥብ በሌላቸው ቀለሞች የተጻፉ ብዙ መጽሓፍትም ስለኣሉ ሰዉ በኣወናባጆች ወደኋላ እየተመለሰ ነው። ይህ የምልክት ቅነሳ ያስከተለው ችግር ነው።
 
===የግዕዝ ቁምፊዎች===