ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 387፦
፳፭. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በስሕተት ኦሮሚፋ 10 እንዚራን ሲያስፈልገው ግዕዝ ሰባት ብቻ ኣለው ይላሉ። ዋየል መደራረብ ትርፉ ስፍራ ማባከን ነው። [http://www.smart-jokes.org/english-spelling-reform.html] ለምሳሌ ያህል “ዸ”ን በኣሥር ዋየሎቹ ለመክተብ ለቁቤ ላቲን 35 ቀለሞች ሲያስፈልጉት ለግዕዙ 15 በቂ ናቸው። ፳፮. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በስሕተት ላቲን 26 ቀለሞች ሲኖሩት [https://www.ascii.cl/htmlcodes.htm] የግዕዙ ብዙ ናቸው ይላሉ። የላቲን "a" ዓይነቶች ከ26 በላይ ናቸው። ዋናዎቹ 26 የላቲን ቀለሞች እንደግዕዙ 37 የተሟሉ ኣይደሉም። ፳፯. ግዕዝ በእጅ ኣይጻፍ ይመስል ስለላቲኑ የእጅ ጽሑፍ (Cursive) የሚያነሱም ኣሉ። ዶክተሩ ኦሮምኛን በግዕዝ ፊደል በኮምፕዩተር ለመክተብ የሚያስፈልጉትን ከሠሩ በኋላ ለ24 ተነባቢና 10 ዋየሎቹ የኦሮምኛ ፊደላቱ 34 ቀለሞችን መፍጠር ስለሚያስቸግርና ኣስፈላጊ ኣይደለም ተብሎ ወደ ላቲን ዞርን ከቀረቡት ምክንያቶች ኣንዱ ነበር። ፳፰. ግዕዝ እንደኦሮሚፋ የኣሉትን (ኩሻዊ) ቋንቋዎችን [https://am.m.wikipedia.org/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB_%E1%89%8B%E1%8A%95%E1%89%8B%E1%8B%8E%E1%89%BD] ጥሩ ኣድርጎ ኣይጽፍም የሚለው ወይም የግዕዝ ኣንድን ድምጽ በኣንድ ቀለም መወከል እንደችግር ተቆጥሮ ወደ ላቲን ለመዞር የቀረቡት ምክንያቶች ወደ እውነት የተጠጉ ኣልነበሩም። ግዕዝ ለኣንድ ድምጽ ኣንድ ቀለምና ኣንድን ቀለም ለኣንድ ድምጽ በማድረግ የተራቀቀ ፊደል ነው።
 
፳፱. በግዕዝና በላቲን የሚጠቀሙ ኢትዮጵያውያን ስለማይግባቡ በየእለቱ እየተራራቁ ናቸው። ኣንድ ሕዝብ በተለያዩ ፊደላትና ቋንቋዎች እንዲጠቀም ማስገደድ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ነበር። ኦሮሞው ዓማርኛ እንዳይማር ተወስኖ የፌዴራል ሥራ እንዳያገኝ ሆኗል። ፴. ኣይርላንዳዊው በርናርድ ሿው ግዕዝን ዓውቆ ቢሆን ኖሮ ላቲን ቦታ ኣይኖረውም ነበር የሚል ጽሑፍ በሰይፉ ኣዳነች ቢሻው እዚህ ቀርቧል። [http://ethiopianege.com/archives/5408] የላቲን ፊደል ለእየኣንድኣንዱ ድምጽ ኣንድ ቀለም እንዲኖረው ተመኝተው ነበር። ላቲን የኣልተሟላና ኣክሳሪ ፊደል መሆኑንም ሿው ገልጸዋል። [http://www.digitalcomposition.org/essays-and-articles/george-bernard-shaw] ፴፩. ላቲን ማወቅ ኦሮሞዎችን ከፊደሉ ተጠቃሚዎች ያቀራርባል ተብሎ እንደምክንያት ቀርቧል። ኢትዮጵያውያን የላቲንን ፊደል ስለሚማሩ ኣልተጎዱም። ፴፪. ግዕዝ ማላልያ የለውም ተብሏል። እንደኣስፈላጊነቱ መጠቀም እንዲቻል የማላልያ (Stretch) ምልክት የዶክተሩ ፓተንትም ውስጥ ተጠቅሷል። [https://patents.google.com/patent/US20090179778A1/en] የዩኒኮድ ግዕዝ መደብም ውስጥ ኣለ። ግዕዝ ኣንድን ቀለም በማጥበቅ፣ በማላላት፣ ሁለቱንም በማድረግ፣ በኣለማድረግና ተራውን በመቀየር በኣምስት ዓይነቶች ያስከትባል ይላሉ ዶክተሩ። ቁቤ ችሎታውን የለውም። ኣንድን የግዕዝ ወይም ላቲን ቀለም በሁለት መተካት ኣይጠቅምም።
 
፴፫. ዶክተሩ ለግዕዝና እንግሊዝኛ ፊደል የሚጠቅሙ ግኝቶችን በማቅረቡ ገፍተውበታል። [http://patft.uspto.gov/netacgi/nph-Parser?Sect1=PTO2&Sect2=HITOFF&p=1&u=%2Fnetahtml%2FPTO%2Fsearch-bool.html&r=1&f=G&l=50&co1=AND&d=PTXT&s1=10133362&OS=10133362&RS=10133362] የኦሮሞ ምሁራን ላቲን እራሱን የኣሻሻለበትን ዘዴዎች እንኳን ሳይጠቀሙ ከግዕዙ ኣጠቃቀም እራሳቸውን ስለኣገለሉ ኢትዮጵያንና ዓለምን እንዳይጠቅሙ እየተደረገ ነው።
 
===ግዕዝና ዓማርኛ===