ከ«የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 1፦
'''የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን''' ከአምስቱ የኦርየንታል (ምስራቃዊ) [[ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ]] አብያተ ክሪስቲያናት አንዱ ነው። [[ኢትዮጵያ]] የ[[ክርስትና]]ን እምነት ከተቀበለችበት ከ[[4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን]] ጀምሮ እስከ [[ጥር 7|ጥር ፮]] ቀን [[1943|፲፱፻፵፫]] ዓ.ም (1951 እ.ኤ.አ.) ድረስ [[የእስክንድርያ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን]] ክፍል ነበር። በ፲፱፻፵፫ ዓ.ም ግን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ባስልዮስ ከእስክንድርያው ፓትርያርክ [[አቡነ ዮሳብ 2ኛ]] የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ 55-60 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው።
 
እባካችሁን፡የተሙአሉ፡አንቀጾች፡ለመጻፍ፡ሞክሩ።
== በታሪክ ==
አመስግናለሁኝ።
 
=== መሠረቶች ===
 
«ተዋሕዶ» ከ[[ልሣነ ግእዝ]] የመነጨ ቃል ሲሆን፡ ትርጒሙም «አንድ ሆኖ» ማለት ነው። ለዚሁም በ[[ዐረብኛ]] ተመሳሳይ ቃል «ታውሒድ» ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል። በ[[ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት]] ቃሉ የሚነካ የክርስቶስ ባሕርይ በ«ሰብዓዊ» እና በ«መለኮታዊ» ተለይቶ ሳይሆን አንድ ብቻ እንደሆነ የሚለው ጽኑ እምነት ነው።
 
በ[[443]] ዓ.ም. (451 እ.ኤ.አ.) በ[[ሮማ]]ው ንጉሥ መርቅያን ዘመነ መንግሥት 650 ኤጲስ ቆጶሳት በተገኙበት የተሰበሰበው የ[[ኬልቄዶን ጉባኤ]] ከሮማው ሊቀ ጳጳሳት [[ቀዳማዊ ልዮን]]"ክርስቶስ ሁለት የተለያዩ ባሕርያት አሉት" የሚል ጽሑፍ አቅርቦላቸው ነበር። ዳሩ ግን የእስክንድርያው ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ "ጌታ ሁለት ባሕርያት አሉት" የሚለው ትምሕርት ስሕተት ነው ብሎ ልዮንን አውገዘው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት በእምነት ተለያዩ። የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ትምሕርት የሚከተሉ ዛሬ የ[[አርሜኒያ]]፣ የ[[ሕንደኬ]]፣ የ[[ግብጽ]]፣ የ[[ሶርያ]]፤ የ[[ኤርትራ]] እና የ[[ኢትዮጵያ]] ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት ናቸው።
 
የቤተክርስቲያን መመስረት በኢትዮጵያ የተጀመረው በወንጌል ሰባኪ [[ቅዱስ ፊልጶስ]] መሆኑ ይታወሳል (ሐዋርያት ምዕራፍ 8)፦
 
:«እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ [[ኢየሩሳሌም]] መጥቶ ነበር...»
 
በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የ[[ትንቢተ ኢሳይያስ]] ክፍል እንዲገባው አስረድቶት በክርስትና አጠመቀው። ንግሥት[[ግርማዊት ህንደኬ 7ኛ]] ከ34 ዓ.ም. እስከ 44 ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።
 
በ4ኛ ምዕተ ዘመን በወንድማማቾቹ በ[[ንጉሥ ኤዛና]] እና በ[[ንጉሥ ሳይዛና]]ዘመን በ[[ፍሬምናጦስ]] አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ «አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን» ተብሎ ይታወቃል። በወጣትነት ዕድሜው ከአጎቱ ከፈላስፋው ከመሮፔዎስ እና ከወንድሙ ከ[[ሲድራኮስ]] ጋራ መርከባቸው ስለሰመጠች ከወንድሙ ጋር ከሞት ተርፈው ምጽዋ አጠገብ ተገኙ። ወደ ንጉሦቹም ግቢ አመጡዋቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበት ደረጃ አገኙ። ንጉስ ኤዛና ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምናጦስን ለኢትዮጵያ አቡነ እንዲሾም ለመጠይቅ ወደ እስክንድርያ ላኩዋቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ [[አትናቴዎስ]] ፍሬምናጦስን ሾሞ ላከው። ፍሬምናጦስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ [[አቡነ ባስልዮስ]] ደግሞ 111ኛው መሆናቸው ነው።
 
=== መካከለኛ ዘመን ===
 
እስላሞች ወደ ግብጽ ከገቡ በኋላ ከእስክንድርያ ጋር የነበረው ግንኙነት ተቸገረ። ጸሐፊው አቡ ሳሊኅ በ12ኛ መቶ ዘመን እንደ ገለጸው፣ ፓትርያርኩ በየዓመቱ 2 ደብዳቤዎች ለኢትዮጵያና ለኖቢያ ነገሥታት ይጽፉ ነበር። ይህንን አደራረግ ግን አቡ ሃኪም አስቀረ። 67ኛው ፓትርያርክ ቂርሎስ እንደ ኤጲስ ቆሞስ የላኩት ሰቨሩስ ሲሆኑ የቤተክርስቲያን ሥራዐት ሁሉ እንዲያስጠበቁ ታዘዙ። በ[[1431]] ዓ.ም. በዓጼ [[ዘርዐ ያዕቆብ]] ዘመን [[አባ ጊዮርጊስ]] ከ1 ፈረንሳያዊ ጐባኝ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስላነጋገሩ አንድ ተልእኮ ወደ [[ሮማ]] ተላከ።
 
በ[[1500]] ዓ.ም. ደግሞ ኢትዮጵያ ከ[[አዳል]] ጋር ስትታገል ማቴዎስ የተባለ አንድ አርሜናዊ ወደ [[ፖርቱጋል]] ተልኮ የፖርቱጋል ንጉሥ እርዳታ ለመነ። ስለዚህ በ[[1512]] ዓ.ም. የፖርቱጋል ሚሲዮን በኢትዮጵያ ደረሰ። በሚከተለው ክፍለ ዘመን ከፖርቱጋል [[ኢየሱሳውያን]] የተባሉ ሚሲዮኖች ቤተ መንግሥቱን ወደ [[ሮማ ካቶሊክ]] ሃይማኖት ለማዞር ብዙ ጣሩ። በመጨረሻ በ[[1617]] ዓ.ም. ንጉሥ [[ሱስንዮስ]] ወደ ሮማ ካቶሊክ እምነት ተቀየሩ። ዳሩ ግን የሮማ ሃይማኖት በተዋህዶ ፈንታ ይፋዊ መሆኑን ሕዝቡ በጣም አልወደደምና በ[[1625]] ሱስንዮስ ዘውዳቸውን ለልጃቸው ለ[[ፋሲለደስ]] እንዲሰጡ ተደረጉ። ፋሲለደስ ወዲያው አገሩን ወደ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መለሱ። ከዚህ በላይ በ[[1626]] ፋሲለደስ ኢየሱሳውያን አገሩን ለቅቀው እንዲሄዱ አዘዙ። በ[[1658]] ዓ.ም. መጻሕፍታቸውን ደግሞ አስቃጠሉ።
 
== ልዩ ባሕርይ ==