ከ«1 እሽመ-ዳጋን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «370px|thumb|እሽመ-ዳጋን የወረሰው የ1 ሻምሺ-አዳድ መንግሥት '''1 እሽመ-ዳጋን''' ከ1688 እስከ 1678 ...»
(No difference)

እትም በ08:20, 21 ፌብሩዌሪ 2011

1 እሽመ-ዳጋን ከ1688 እስከ 1678 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር[1]) የአሦር ንጉሥ ነበረ። አባቱ 1 ሻምሺ-አዳድ የአሦር ንጉሥ እየሆነ፣ ልጁን እስመ-ዳጋንን በኤካላቱም ዙፋን ላይ አስቀምጦት ነበር። ታናሹ ወንድሙ ያስማሕ-አዳድ ደግሞ የማሪን ዙፋን ተቀበለው። በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ 17ኛው አመት (በ1688 ዓክልበ.) 1 ሻምሺ-አዳድ እንደ ሞቱ ልጁም እሽመ-ዳጋን የአሦርን መንግሥት እንደ ወረሰው ይታወቃል።

እሽመ-ዳጋን የወረሰው የ1 ሻምሺ-አዳድ መንግሥት

በዘመኑ መጀመርያ፣ የሆራውያን ቱሩኩ ጎሣ አለቃ ሊዳይ ጽኑ አመጽ በሹሻራ አገር አስነሣሣ። ክፍላገሩ በተለይ ተራራማ ስለ ሆነ፣ እሽመ-ዳጋን የአሦርን ሠራዊት ሹሻራን እንዲተው አደረገ። ከዚያ ግን ኡታን አገር አሸነፈ። በተሸነፈው አገር በኡታ ሥልጣኑን ለመጠብቅ፣ ወንድሙን ያስማሕ-አዳድ ከማሪ ወደ ኡታ እንደራሴነት አዛወረው። በስደት የኖረው የማሪ ቀድሞ ንጉስ ዚምሪ-ሊም በዚያ ዕድሉን አገኝቶ ማሪን ከያስማሕ-አዳድ ነጥቆ ወደ ዙፋኑ ተመለሰ።

በእሽመ-ዳጋን ዘመን፣ አሦር ከማሪ፣ ከኤሽኑና እና ከኤላም ጋራ ጦርነት ያደርግ ነበር። ስለዚህ እሽመ-ዳጋን ከበፊቱ ጠላቶች ከቱሩኩ ሕዝብ ጋር የስምምነት ውል አደረገ። የቱሩኩ አለቃ ሴት ልጅ ለእሽመ-ዳጋን ወንድ ልጅ ለሙት-አሽኩር ታጨች። በዚህ ወቅት ደግሞ የባቢሎን ሃይል እየበረታ አሦር ከባቢሎን ወዳጅነት ተጠቀመ። ሆኖም እሽመ-ዳጋን የአባቱን ግዛት በሙሉ ሊጠብቅ አልተቻለውም። በመጨረሻ ግዛቱ የኤካላቱም፣ አሹርነነዌ ከተሞች ዙሪያ ብቻ ያጠቅልል ነበር።

ማሪ ጽሑፎች እንደሚዘገብ፣ በዚምሪ-ሊም 9ኛው አመት (በ1679 ዓክልበ.)፣ ኤላማውያን እሽመ-ዳጋንን ከአገሩ አባረሩትና ወደ ባቢሎን ሸሸ። በዚያ በጽናት ታመመ። እሽመ-ዳጋን ማዕረጉን በይፋ ቢጠብቅም የሃሙራቢን ሥልጣን እንዲቀብል ተገደደ። በመሞቱም አሦር በብሔራዊ ሁከት ተያዘ፤ ልጁ ሙት-አሽኩር ይቅርና ብዙ ሌሎች ሰዎች ዙፋኑን ለመያዝ ሞከሩ። ከነዚህም አሹር-ዱጉል አገሩን ለጥቂት አመት እንዲገዛ በቃ።

የአሦር ነገሥታት ዝርዝር እሽመ-ዳጋን ለ40 አመት እንደ ነገሠ ሲል፣ ባለፈው ቅርብ ጊዜ ግን (1995 ዓ.ም.) ተጨማሪ ሰነዶች በካነሽ (በዛሬው ቱርክ) በመገኘታቸው አሁን የአሦር ንጉሥ ለ11 ዓመታት ብቻ እንደ ነበር ይታወቃል።[2]

ዋቢ መጽሐፍት

  1. ^ http://chronosynchro.net/base.php?page=accueil (ፈረንሳይኛ)
  2. ^ http://chronosynchro.net/base.php?page=accueil (ፈረንሳይኛ)
  • Jean-Marie Durand, Documents Epistolaires du Palais de Mari, Collection « Littérature Ancienne du Proche-Orient » N° 16. (1997); (2002) ISBN 2204056855 (ፈረንሳይኛ)