ከ«ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 5፦
አካለ መጠን ሲደርሱ በ፲፰ዓ መታቸው በ[[1925|፲፱፻፳፭]] ዓ.ም. [[አዲስ አበባ]] በ[[ክብር ዘበኛ]] ደንብ ተቀጥረው ወዲያው በ[[ቀኅሥ|ንጉሠ ነገሥቱ]] ትዕዛዝ ከስድሳ ዘጠኝ አዲስ ወታደሮች ጋር [[ባሌ]] ተመድበው እስከ [[1927|፲፱፻፳፯]] ዓ.ም ድረስ በተራ ወታደርነት ከዚያም በ ሃምሳ ዓለቃና በባሻነት ማእረግ ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ [[ኢጣሊያ]] [[ኢትዮጵያ]]ን ሊወር ሲመጣ በ[[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም በምስራቅ ደቡብ በ[[ደጃዝማች በየነ መርዕድ]] እና በ[[ጄነራል አስፋው ወልደ ጊዮርጊስ]] መሪነት፤ የመጀመሪያ ልጃቸው ዓለማየሁ በተወለደ በዘጠኝ ቀኑ፤ [[ጥቅምት 11|ጥቅምት ፲፩]] ቀን [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም ከ[[ጎባ]] ወደ [[ኦጋዴን]] ዘመቱ።
በዚህ ጦር ግንባር ፱ ወራት [[ለበሽሊንዲ]]፤ [[ዋቢ ሸበሌ]]፤ እና የመሳሰሉ ሥፍራዎች ከ እነ [[ባላምባራስ አየለ ወልደማርያም]] ጋር ሆነው ጠላትን ሲከላከሉ ከርመው ወደ ጎባ ተመለሱ። ከ[[ሰኔ]] [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም ጀምሮ እስከ [[ሚያዝያ 23|ሚያዚያ ፳፫]] ቀን [[1929|፲፱፻፳፱]] ዓ.ም
ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ከተቀላቀሉ በኋላም በ[[ደንዲ]]፤ በ[[ሶዶ]]፤ በ[[በዳቄሮ]] እና በመሳስሉ ሥፍራዎች አርበኝነታቸውን እስከ [[ጥቅምት]] [[1931|፲፱፻፴፩]] ዓ.ም ድረስ ሲያካሂዱ ከቆዮ በኋላ በዳቄሮ ከሚባለው ሥፍራ ላይ ከ [[ዱካ ዳኦስታ]]ና ከ [[ጄነራል ናዚ]] ተልኬያለሁ የሚለው [[ሙሴ ቀስተኛ]](ሴባስቲያኖ ካስታኛ) (''Sebastiano Castagna'') የሚባለው ሰላይ ከሦሥት ባላባቶች ጋራ መጣ። አርበኞቹም ቀደም ሲል በ[[1930|፲፱፻፴]] ዓ.ም ይኼው ሰላይ ወደ ባላምባራስ [[አበበ አረጋይ]] ዘንድ ሄዶ የጦሩን ኃይል ከአየ በኋላ ብዙ አርበኛ እንዳስፈጀ ሰምተው ስለነበር እነሱንም እንደዚሁ ለማስፈጀት እንደመጣ ስለተገንዘቡት ባሻ ኪዳኔ ወልደመድኅን በመውዜር ጠመንጃ ሲመቱት 'ማማ ሚያ፤ ኢጣልያ ለዘለዓለም ትኑር ለኢጣሊያ ስል ሞትኩላት' ብሎ ሲናገር በሽጉጥ ራሱን መትተው ከገደሉት በኋላ የለበሰውን ሙሉ ገበርዲን ልብስና ካፖርት እንዲሁም የ [[ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ]] ን ስዕል ያለበትን የብር ሰዐትና በቅሎውን ከነኮርቻው ማረኩት። እሱም እንደተገደለ አብረውት መጥተው የነበሩት ባላባቶች ለጄነራል ናዚ አስታውቀው ኖሮ ያያ አምሥት ባታሊዮን ወታደርና ሃያ ስምንት አውሮፕላን ወደበዳቄሮ ዘምቶ ተርታውን ለሦሥት ቀን ሲከላከሉ ከቆዩ በኋላ አርበኞቹ ተሸንፈው ጠላትም የሙሴ ቀስተኛን እሬሳ አንስቶ ወሰደ። አርበኞቹም ከዚያ ሥፍራ ሸሽተው ሶዶ ላይ እንደገና ልስምንት ቀን ተዋጉ።
|