ከ«ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 5፦
አካለ መጠን ሲደርሱ በ፲፰ዓ መታቸው በ[[1925|፲፱፻፳፭]] ዓ.ም. [[አዲስ አበባ]] በ[[ክብር ዘበኛ]] ደንብ ተቀጥረው ወዲያው በ[[ቀኅሥ|ንጉሠ ነገሥቱ]] ትዕዛዝ ከስድሳ ዘጠኝ አዲስ ወታደሮች ጋር [[ባሌ]] ተመድበው እስከ [[1927|፲፱፻፳፯]] ዓ.ም ድረስ በተራ ወታደርነት ከዚያም በ ሃምሳ ዓለቃና በባሻነት ማእረግ ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ [[ኢጣሊያ]] [[ኢትዮጵያ]]ን ሊወር ሲመጣ በ[[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም በምስራቅ ደቡብ በ[[ደጃዝማች በየነ መርዕድ]] እና በ[[ጄነራል አስፋው ወልደ ጊዮርጊስ]] መሪነት፤ የመጀመሪያ ልጃቸው ዓለማየሁ በተወለደ በዘጠኝ ቀኑ፤ [[ጥቅምት 11|ጥቅምት ፲፩]] ቀን [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም ከ[[ጎባ]] ወደ [[ኦጋዴን]] ዘመቱ።
 
በዚህ ጦር ግንባር ፱ ወራት [[ለበሽሊንዲ]]፤ [[ዋቢ ሸበሌ]]፤ እና የመሳሰሉ ሥፍራዎች ከ እነ [[ባላምባራስ አየለ ወልደማርያም]] ጋር ሆነው ጠላትን ሲከላከሉ ከርመው ወደ ጎባ ተመለሱ። ከ[[ሰኔ]] [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም ጀምሮ እስከ [[ሚያዝያ 23|ሚያዚያ ፳፫]] ቀን [[1929|፲፱፻፳፱]] ዓ.ም ድረስ ከ[[አሩሲ]]፤ ከ[[ሲዳሞ]]፤ ከ[[ሐረር]]ና [[ኦጋዴን]] ወደ [[ጎባ]] በሃይል የመጣውን የጠላት ጦር በራሳቸው መሪነት ሲዋጉ ከርመው፤ መጨረሻ ላይ ተማም ከሚባለው ሥፍራ ላይ በተካሄደው ጦርነት ላይ ማምለጥ በማይቻልበት ኹኔታ በጠላት እጅ ወደቀው ተማረኩ። ጠላትም ለአምስት ወራት በጽኑ እሥራት ከያዛቸው በኋላ፤ በ[[ጥር]] ወር [[1930|፲፱፻፴]] ዓ.ም ጣሊያን መሳሪያ አስታጥቆ በሽፍን መኪና ከጎባ [[ወሊሶ]] አምጥቶ እስር ላይ አዋላቸው። ባሻ ኪዳኔም እዚሁ እስር ቤት እያሉ አብረዋቸው ከታሰሩት መሀል በምስጢር ቃለ መሃላ በመስጠት መቶ ሰዎች አሳብረው እዚያ ያለውን የጠላት ጦር ፈጅተው ለመሸፈት ከወሰኑ በኋላ ወደ ባላምባራስ (በኋላ ደጃዝማች) [[ገረሱ ዱኪ]] የሚላክ ሰው በማፈላለግ ላይ እያሉ ጠላት ሰምቶ ኖሮ አጥብቆ ይከታታላቸው ጀመር። ይኼን ሲገነዘቡ ነገሩን አብርደው ሲጠባበቁ ወደ ባላምባራስ ገረሱ የላኩት ብሩ የሚባለው መልክተኛ [[ጥር 15|ጥር ፲፭]] ቀን [[1930|፲፱፻፴ ]]ዓ.ም በጠላት እጅ ተይዞ ቀኑን ሙሉ ሲመረመር ዋለ። ባሻ ኪዳኔም በዚያው ዕልት ከምሽቱ ፪ ሰዐት ሲሆን በቃለ መሃላ ያደራጇቸውን ሰዎች በያሉበት እየሄዱ ከነመሳሪያቸው እየሰበሰቡ ሲያከማቹ የጠላትም ዘቦች ነቅተው በተንቀቅ ተሰልፈው ይጠብቋቸው ጀመር። ባሻ ኪዳኔ ግን ወገኖቻቸውን ሸልሉ ብለው ሲያሸልሉ የጠላት ዘቦች ተደናግጠው እንዲያውም 'እነሱ ሳይተኩሱ አትተኩሱ' የሚል ትእዛዝ አስተላልፈው ይጠባበቃሉ። ባሻ ኪዳኔም በዚህ ጊዜ ቃለ መሓላ ከሰጧቸው ፻ ሰዎች ውስጥ ፶፭ ወታደር ከነመሳሪያው፤ አራት ድግን መትረየስ፤ አስር ሣጥን ጥይት፤ ስድስት ሽጉጥ ከጠላት እጅ ነጥቀው እየተታኮሱ ሲወጡ የጠላት ኃይል ሃያ ወታደርና አንድ መትረየስ ከ ሁለት ሣጥን ጥይት ጋር ብቻ ገንጥሎ ሲያስቀርባቸው የተረፈውን መሳሪያና ወታደሮች ጋር ድል አድርገው ሸፈቱ። ወዲያውም ኩሳ ኪዳነምሕረት ከሚባል ሥፍራ ላይ ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ተገናኙ።
 
ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ከተቀላቀሉ በኋላም በ[[ደንዲ]]፤ በ[[ሶዶ]]፤ በ[[በዳቄሮ]] እና በመሳስሉ ሥፍራዎች አርበኝነታቸውን እስከ [[ጥቅምት]] [[1931|፲፱፻፴፩]] ዓ.ም ድረስ ሲያካሂዱ ከቆዮ በኋላ በዳቄሮ ከሚባለው ሥፍራ ላይ ከ [[ዱካ ዳኦስታ]]ና ከ [[ጄነራል ናዚ]] ተልኬያለሁ የሚለው [[ሙሴ ቀስተኛ]](ሴባስቲያኖ ካስታኛ) (''Sebastiano Castagna'') የሚባለው ሰላይ ከሦሥት ባላባቶች ጋራ መጣ። አርበኞቹም ቀደም ሲል በ[[1930|፲፱፻፴]] ዓ.ም ይኼው ሰላይ ወደ ባላምባራስ [[አበበ አረጋይ]] ዘንድ ሄዶ የጦሩን ኃይል ከአየ በኋላ ብዙ አርበኛ እንዳስፈጀ ሰምተው ስለነበር እነሱንም እንደዚሁ ለማስፈጀት እንደመጣ ስለተገንዘቡት ባሻ ኪዳኔ ወልደመድኅን በመውዜር ጠመንጃ ሲመቱት 'ማማ ሚያ፤ ኢጣልያ ለዘለዓለም ትኑር ለኢጣሊያ ስል ሞትኩላት' ብሎ ሲናገር በሽጉጥ ራሱን መትተው ከገደሉት በኋላ የለበሰውን ሙሉ ገበርዲን ልብስና ካፖርት እንዲሁም የ [[ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ]] ን ስዕል ያለበትን የብር ሰዐትና በቅሎውን ከነኮርቻው ማረኩት። እሱም እንደተገደለ አብረውት መጥተው የነበሩት ባላባቶች ለጄነራል ናዚ አስታውቀው ኖሮ ያያ አምሥት ባታሊዮን ወታደርና ሃያ ስምንት አውሮፕላን ወደበዳቄሮ ዘምቶ ተርታውን ለሦሥት ቀን ሲከላከሉ ከቆዩ በኋላ አርበኞቹ ተሸንፈው ጠላትም የሙሴ ቀስተኛን እሬሳ አንስቶ ወሰደ። አርበኞቹም ከዚያ ሥፍራ ሸሽተው ሶዶ ላይ እንደገና ልስምንት ቀን ተዋጉ።