ከ«ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 57፦
በሦስተና ደረጃ የኤርትራን የኅብረት መንግሥት በተመለከት የንጉሠ ነገሥቱ ተግሳጽ በሌሎች (ተቃዋሚዎቻቸው) ፊት ሲደርሳቸው ጆን ማርካኪስ “በ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] የአስተዳደር ስልት፤ ለሥልጣን የብቃተ ቢስነት ወንጀል ወይም የማይካድ የሙስና ድርጊት ሲታይ የተለመደው ቅጣት ወደሌላ ሥራ መዛወር ሲሆን፤ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝ አለመሆን ግን ያለምንም ጥርጣሬ በፈጣን ፍርድ በግዞት ዓለም መጥፋትን ያስከትላል።” ያለን በፀሐፌ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስው ላይ እየተተገበረ መሆኑን እንገነዘባለን።
 
ወዲያውኑ ፀሐፌ ትዕዛዝ ከጽሕፈት ሚኒስቴርነታቸው ተሽረው መጀመሪያ የ[[አርሲ|አሩሲ]] ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ ሆነው እስከ [[1953|፲፱፻፶፫]] ዓ/ም ከቆዩ በኋላ ወደ [[ጋሞጐፋ ዞን|ገሙ ጎፋ]] ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳድሪ ሆነው ተዛወሩ።
 
የስድሳ ስድስቱ አብዮት ኃይለ ሥላሴን ከሥልጣን ከማውርደኡ ከጥቂት ጊዜ ቀደም ብሎ ለሕክምና ወደ እንግሊዝ አገር ይሄዱና ሁለተኛውንና የመጨረሻውን የስደት ዘመን ጀምረው በተወለዱ በሰባ አምስት ዓመታቸው እዚያው እንግሊዝ አገር አርፈው ተቀበሩ።