ከ«ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 11፦
ባሻ ኪዳኔ ከባላምባራስ ገረሱ ጋር ከሙሴ ቀስተኛ የተማረከውን አላስረክብም በማለታቸውና በሌላም ምክንያቶች ባለመስማማታቸው፤ በ[[ኅዳር]] ወር [[፲፱፻፴፩]] ዓ.ም. አባሎቻቸውን አስከትለው ወደ ትውልድ አገራቸው ወደቡልጋ ተጉዘው በአሥራ ሁለት ቀናቸውም ቡልጋ ገቡ። እዚሁም ከ[[ፊታውራሪ ኃይለማርያም ማናህሌ]] እና ከ[[ፊታውራሪ ተረፈ ማናህሌ]] ጋር ተቀላቅለው እስከ [[መጋቢት]] [[1931|፲፱፻፴፩]] ዓ.ም. ድረስ በውሽንግር፤ ጨፌ ዶንሳ ምሽግ፤ ነጭ ድንጋይ ምሽግ፤ ልዝብ ድንጋይ ከተባሉ ቦታዎች ላይ ከጠላት ኃይል ጋር ሲዋጉ ከርመው በመጋቢት ወር በሃገሩ ላይ ገብቶ በነበረው የ [[እንቅጥቅጥ በሽታ]] በጽኑ ታመው ከልዝብ ድንጋይ ምሽግና ቤቶች ነጭ ድንጋይ ጦስኝ ምሽግ ከወደምስራቅ ኮረማሽ መካከል ታመው ተኙ:: ወዲያው በሰኔ ወር ሦሥት አምባ ላይ ሰፍረው ሳሉ ጠላት በ[[ሦስት አምባ]]፤ በ[[ወይን አምባ]] እና በ[[ጦስኝ]] በኩል ወርዶ ሲከባቸው ባሻ ኪዳኔ ገመምተኛ ስለነበሩ መሮጥ አቅቷቸው ‘ተማረክ’ እያለ የከበባቸውን የጠላት ጦር እየተከላለከሉ ጫካ ገቡ የጠላትም ወታደሮች የገቡበት ጠፍቶባቸው ሲፈልጉ ባሻ ኪዳኔ ጎርፍ በጀለጣት ዛፍ ተንጠልጥለው ደፍጠው ሲጠባበቁ ጠላት ጫካውን በእሳት ነበልባል ግራና ቀኙን ሲያቃጥልው እሳቸው ያሉባት ሳትቃጠል ሊተርፉ ቻሉ። ከሦስት ቀንም በኋላ ጠላት ለቆ ሲሄድ ባሻ ኪዳኔ ከጅረት ወርደው ውሃ ሲጠጡ ደክመው ወድቀው ሳሉ ወንድማቸውና ሌሎች ሲፈልጓቸው በጥይት ያሉበትን አሳወቋቸውና መጥተው በቃሬዛ አዛውሯቸው፡
 
ከዚህ በኋላ ክረምቱን ቡልጋ ውስጥ በ[[ነጭ ድንጋይ]]፤ [[ፍልፍል አፈር]]፤ [[ጦስኝ ምሽግ]]፤ በ[[መስኖ]] ከነ[[ደጃዝማች ሀብተ ሥላሴ]]፤ ከነ[[ፊታውራሪ በለጠ ሳሴ]]ና [[ፊታውራሪ አጎናፍር]] ሌሎችም ስመጥሩ የቡልጋ ልጆች ጋር ሆነው ጠላትን ሲያጠቁና ሲከላከሉ ቆይተው በ[[መስከረም]] [[1932|፲፱፻፴፪]] ዓ.ም በ[[ሰገሌ]] በኩል ተጉዘው [[ገሊላ]] ከሚባል ሥፍራ ላይ ከራስ አበበ አረጋይ ጋር ሲቀላቀሉ ባሻ ኪዳኔ የ[[ግራዝማች]]ነት ማእረግማዕረግ ተሾሙ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከ”[[ጊዲዮን ፎርስ]]” (Gideon Force) ጋር ወደ[[ጎጃም]]ና ወደ[[ጎንደር]] እስከዘመቱ [[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ.ም ድረስ ከራስ አበበ ጋር ጠላትን በየቦታው ሲዋጉ በአርበኝነት ቆዩ። ከብዙ ከተለያዩ ውጊያዎችና ጀብዱዎች በኋላ በ[[የካቲት]] [[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ.ም [[መሶቢት]] ከሚባለው ቦታ ላይ በመሪነት የጠላትን ጦር ድል አድርገው ወደዋናው ሰራዊት ከተቀላቀሉ በኋላ ራስ አበበ የ[[ቀኛዝማች]]ነት ማእረግማዕረግ ሾሟቸው።
 
===የሰሜን ዘመቻ===
መስመር፡ 25፦
[[የካቲት 18|የካቲት ፲፰]] ቀን [[1934|፲፱፻፴፬ ]]ዓ.ም የ[[ፊታውራሪ]]ነት ማእረግ ተሰጥተው መጀመሪያ በ ወረዳ አስተዳዳሪነት ከዚያም በ[[1936|፲፱፻፴፮]] ዓ.ም የ[[የጁ]]፤ የ[[ዋድላ ደላንታ]]፤ የ[[መቂት]]፤ የ[[ሸደሃ]]ና የ[[ዳውንት]] [[ብሔራዊ ጦር]] አዛዥና የጠቅላይ ግዛቱ ጦር አማካሪ ከዚያም እስከ [[1943|፲፱፻፵፫]] ዓ.ም ድረስ በወሎና በ[[ከፋ]] ውስጥ አውራጃ አስተዳዳሪነት ተመድበው ሲያገለግሉ ቆዩ።
 
[[ከፋ]] ውስጥ እንደተሾሙ (፲፱፻፵፫ ዓ.ም) ከጠቅላይ ገዢው ጋር ባለመስማማታቸው ተሽረው ንጉሠ ነገሥቱ ከስልጣን እስከወረዱ ድረስ በእስራትና በግዞት ሃያሐያ ሦስት ዓመት ሙሉ ለሃገሩ እንዳልተጋደለ፣ በአርበኝነት ደሙን እንዳላፈሰሰ፣ ለኢትዮጵያ ነጻነት መስዋዕት እንዳልሆነ ተቆጥረው፣ ንጉሠ ነገሥቱ ለቅርብ ሎሌአቸው አድልተው ደጃዝማች ኪዳኔን ከሀገር አገልግሎት አስወገዷቸው።
 
ንጉሠ ነገሥቱ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ደጃዝማች ኪዳኔ በመላ [[የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር]] ሊቀመንበርነት ተመርጠው ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ ሃገራቸውንንና ማኅበሩን ወክለው [[ሮማ]] ላይ በተካኼደው የዓለም አቀፍ ጸረ ኑክሊየር መሣሪያ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ሲጓዙ [[መስኮብ]] (Moscow) ላይ [[ጥቅምት 9|ጥቅምት ፱]] ቀን [[1972|፲፱፻፸፪]] ዓ.ም. በተወለዱ በስልሳ አራት ዓመታቸው አረፉ። ቀብራቸውም [[መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን]] [[ጥቅምት 15|ጥቅምት ፲፭]] ቀን ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. ተከናውኗል።