ከ«ጳውሎስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «ዕብራዊ ስሙ ሳውል ሮማዊ ስሙ ጳውሎስ በተርሴስ (ዛሬ በቱርክ ውስጥ) ከሚቀመጥ ከአንድ ሸማኔ ተወልዶ ...»
 
No edit summary
መስመር፡ 8፦
:ሳውል፦ ምን እንዳደርግ፤ ትፈቅዳለህ።
:ኢየሱስ፦ ወደ ደማስቆ ከተማ ግባ፤ ልታደርገው የሚገባህን [[ሐናንያ]] ይነግርሃል።
:::::::::::::::የሐዋ፡ሥራ፡ም፡ ፱።
 
በዚህ ዓይነት ጳውሎስ ክርስትናን የተቀበለው ከክርስቶስ ነው ማለት ይቻላል። ዝርዝር ነገር ከሐናንያ ማጥናቱ እርግጥ ነው። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ፍጹም ክርስቲያን፤ ትጉህ ሐዋርያ ሆነ። ያለ ዕረፍት የግሪኮችና የሮማውያን አማልክት እነዘውስ እነአርጤሚስ የአሶራውያንና የሲዶናውያን አማልክት እነአስታርት እነበዓል የገነኑባቸውን ከተሞች ያለዕረፍት እየዞረ የነዚያን ከንቱነት፤ የክርስቶስን አዳኝነት በቃልም፤ በጽሕፈትም መሰከረ። ለአባቶቹ ለዕብራውያንም በብሉይ ሐዲስ መተካቱን ለመንገር አልፈራም። ስለክርስቶስና ስለወንጌል በኢየሩሳሌም ተገረፈ፤ በቂሣርያ ታሠረ፤ በሮማ በሰይፍ አንገቱን ተቆርጦ ሞተ።
 
ነገር ግን በደረሰባቸው ከተሞች ሁሉ ክርስቶስን ሳያሳምን ቤተ ክርስቲያን ሳይመሠርት አያልፍም ነበር። ፲፬ መልዕክቶችን ሲጽፍ፤ ከኢየሩሳሌም ግሪክ፤ ከግሪክ ሮማ፤ እየተመላለሰ የሐዋርያነት ሥራውን ሲያከናውን ራሱ ድንኳን እየሰፋ የራሱን መሮሪያ ራሱ ይችል ነበር እንጂ ከሰው ድካም የመነጨ ወይንና ምግብ በርሱ፤ ጉሮሮ አላለፉም ማለት ነው። ደንበኛ ሐዋርያነቱን ከሚያስረዱት ከብዙ ሥራዎቹ ውስጥ አንደኛው ይህ ነው።
 
[[መደብ:ክርስትና]]