ሉሳካዛምቢያ ዋና ከተማ ነው።

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር ከነአካባቢው 1,773,300 ሆኖ ሲገመት ከተማው ብቻውን 1,265,000 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 15°26′ ደቡብ ኬክሮስ እና 28°20′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

1897 ዓ.ም. ሉሳካ ለአለቃው ሉሳካ ተሰይሞ በአውሮፓውያን የተስፋፋ መንደር ነበረ። በ1927 ዓ.ም. የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስሜን ሮዴዝያ መቀመጫ ወዲህ ከሊቪንግስቶን ተዛወረ። በ1957 ዓ.ም. ዛምቢያ ነጻነት ሲያገኝ የዛምቢያ ዋና ከተማ ሆነ።