The Abbott and Costello Show (ዘ አቦት ኤንድ ኮስተሎ ሾው) ከ1952 እስከ 1954 እ.ኤ.አ. ድረስ የተሠራ አስቂኝ አሜሪካዊ ትርዒት ነበር። ሁለቱ የቀልድ ባለሙያዎች በድ አቦት እና ሉ ኮስተሎ በትርዒቱ ውስጥ በሎስ አንጀሌስ ከተማ ሥራ ፈት ተዋናዮች እና አዳባዮች ናቸው። በሁለት አመት ላይ 52 ክፍሎች ተሠሩ፣ እያንዳንዱም በ30 ደቂቃ ውስጥ የሚታይ ነው።

አቦት እና ኮስተሎ

ይሄው ትርዒት በዓለም ዙሪያ በብዙ አገራት በኢትዮጵያም ስለ ተሠራጨ፣ እጅግ ዝነኛ የአሜሪካ ኪነት አስተዋጽኦ ሆኖ ይቆጠራል።