ግም ግም ሲል

(38)ሊቁ ገብረሀና በሀያ ስድስት ዓመታቸው ጎንደር ውስጥ ሊቀ ካህናት ሆነው ተሾሙ። በዚህ ጊዜ አንዲት ጎንደሬ ዘንድ ጠበል ተጠርተው ቢሄዱ የሚወጡት ሰዎች ሁሉ «ጠላው ጥሩ አይደለም» ሲሉ ይሰሙና ተመልሰው ወደቤታቸው ይሄዳሉ። ሴትዮዋም በመቅረታቸው አዝና ቤታቸው ሄዳ «ምነው አባ ጠበል ጠርቼዎት ሳይመጡ ቀሩ?» ብትላቸው “ኧረ መጥቼ ሰው ግም ግም ሲል ጊዜ ነው የተመለስኩት።” አሏት።