ጌታሁን ጋረደው

የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ

ጌታሁን ጋረደው ወዳጄ የኢፌዲሪ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው በማገልገል ላይ ያሉ ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኛ ናቸው። ጌታሁን የወላይታ ተወላጅ ሲሆን በ2018 የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን አገልግሏል።[1]

ጌታሁን ጋረደው
የኢፌድሪ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር
2014
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር
ከሰኔ 2010ዓ.ም. እሰከ ህዳር 2011ዓ.ም.
ቀዳሚ አስራት ጤራ
ተከታይ ዳጋቶ ኩምቤ
የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ
ህዳር 2011ዓ.ም. እስከ ግንቦት 2014ዓ.ም.
የኢፌድሪ ትምህርት ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ
ግንቦት 2014ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 2015ዓ.ም.
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የተፈጥሮ ሀብት ማኔጅመንት ዲን
2001ዓ.ም. እስከ 2008 ዓ.ም.
የተወለዱት ቦዲቲኢትዮጵያ
የፖለቲካ ፓርቲ ብልፅግና ፓርቲ
ዜግነት ኢትዮጵያዊ
ሀይማኖት ጴንጤቆስጤያዊ ክርስትና
ማዕረግ ዶ/ር

ሙያ ለማስተካከል

ከ2009 እስከ 2016 ጌታሁን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ በረዳት ፕሮፌሰርነት፣ የአካዳሚክ ዲን፣ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ኦፊሰር እና የተፈጥሮ ሀብት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል። ከጁላይ 2018 እስከ ህዳር ወር ድረስ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ሰርተዋል። ጌታሁን ከሰኔ 2020 እስከ ህዳር 2022 የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው አገልግለዋል።[2] በምክትል ፕሬዝደንትነት ማዕረግም የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮን ከ2018 ጀምሮ ለአራት ዓመታት መርተዋል። አሁን በፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ አቶ ጌታሁን ጋረደው የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው እየሰሩ ነው።[3]

ዋቢ ለማስተካከል