ብ/ጄኔራል ዶ/ር ጋጋ አልጆ በደቡብ ኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው የጦር ጄኔራልና ዶክተርም ጭምር ለመሆኑ የበቁ ምሁር ሲሆኑ በጭንቅላት ካንሰር ምክንያት በ64 ዓመታቸው በፈረንጆች አቆጣጠር በ1997 በሞት ተለይተዋል። ትውልዳቸው ከወደወላይታ ነው፡፡ ብ/ጄነራል ጋጋ ከዮጎዝላቭያ ተወላጅ ከሆኑት ባለቤታቸው የአንዲት ሴት ልጅ አባት ነበሩ።