የኢትዮጵያና የጅቡቲ የምድር ባቡር ድርጅት

የኢትዮጵያና የጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት (የቀድሞው ፍራንኮ-ኢትዮጵያ ምድር ባቡር ድርጅት) የ784 ኪ.ሜ ርዝመት ብቸኛና ባለ አንድ መስመር ሲሆን ይህ መስመር የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባንና ጅቡቲ ከተማን የሚያያይዝ ነው። ከሐያ ዓመታት አድካሚ ስራ በኋላ በ1911 ተሰርቶ ተመርቋል።