የሐዋርያት ሥራ ፯ በአዲስ ኪዳን ፭ኛ መጽሐፍ "የሐዋርያት ሥራ" ውስጥ የሚገኝ ሲሆን "ስባተኛው ምዕራፍ" ነው ። የሚያተኩረውም በቀዳሚ ሰማዕት ቅዲስ እስጢፋኖስ የመንፈሳዊ ተጋድሎ ሥራዎች ላይ ፣ የሥላሴ ምስክርነት ላይና ሰማዕትነት ነው ። ይህም በ፷ "ስልሳ" ንዑስ ክፍሎች ይካተታል ።

የሐዋርያት ሥራ ፯
የቅዱስ እስጢፋኖስ ወግረት
አጭር መግለጫ
ፀሐፊ ቅዱስ ሉቃስ
የመጽሐፍ ዐርስት የሐዋርያት ሥራ
የሚገኘው በአዲስ ኪዳን ፭ኛው መጽሐፍ
መደብ የቤተክርስቲያን ታሪክ

የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፯

ቁጥር ፩ - ፲ ለማስተካከል

 1፤ሊቀ፡ካህናቱም፦ይህ፡ነገር፡እንዲህ፡ነውን፧አለው፤ 2፤ርሱም፡እንዲህ፡አለ፦ወንድሞችና፡አባቶች፡ሆይ፥ስሙ።የክብር፡አምላክ፡ለአባታችን፡ለአብርሃም፡ በካራን፡ሳይቀመጥ፡ገና፡በኹለት፡ወንዝ፡መካከል፡ሳለ፡ታየና፦ 3፤ከአገርኽና፡ከዘመዶችኽም፡ወጥተኽ፡ወደማሳይኽ፡ወደ፡ማንኛውም፡ምድር፡ና፡አለው። 4፤በዚያን፡ጊዜ፡ከከለዳውያን፡አገር፡ወጥቶ፡በካራን፡ተቀመጠ።ከዚያም፡አባቱ፡ከሞተ፡በዃላ፡እናንተ፡ዛሬ፡ ወደምትኖሩባት፡ወደዚች፡አገር፡አወጣው። 5፤በዚችም፡የእግር፡ጫማ፡ስንኳ፡የሚያኽል፡ርስት፡አልሰጠውም፤ነገር፡ግን፥ልጅ፡ሳይኖረው፡ለርሱ፡ ከርሱም፡በዃላ፡ለዘሩ፡ርስት፡አድርጎ፡ይሰጠው፡ዘንድ፡ተስፋ፡ሰጠው። 6፤እግዚአብሔርም፡ዘሩ፡በሌላ፡አገር፡መጻተኛዎች፡እንዲኾኑ፡አራት፡መቶ፡ዓመትም፡ባሪያዎች፡ እንዲያደርጓቸው፡እንዲያስጨንቋቸውም፡እንዲህ፡ተናገረ፤ 7፤ደግሞም፡እግዚአብሔር፦እንደ፡ባሪያዎች፡በሚገዟቸው፡ሕዝብ፡ላይ፡እኔ፡እፈርድባቸዋለኹ፥ከዚህም፡ በዃላ፡ይወጣሉ፡በዚህም፡ስፍራ፡ያመልኩኛል፡አለ። 8፤የመገረዝንም፡ኪዳን፡ሰጠው፤እንዲሁም፡ይሥሐቅን፡ወለደ፡በስምንተኛውም፡ቀን፡ገረዘው፡ይሥሐቅም፡ ያዕቆብን፡ያዕቆብም፡ዐሥራ፡ኹለቱን፡የአባቶችን፡አለቃዎች። 9፤የአባቶችም፡አለቃዎች፡በዮሴፍ፡ቀንተው፡ወደ፡ግብጽ፡ሸጡት፤እግዚአብሔርም፡ከርሱ፡ጋራ፡ነበረ፥ 10፤ከመከራውም፡ዅሉ፡አወጣው፥በግብጽ፡ንጉሥ፡በፈርዖንም፡ፊት፡ሞገስንና፡ጥበብን፡ሰጠው፥በግብጽና፡ በቤቱ፡ዅሉ፡ላይም፡ቢትወደድ፡አድርጎ፡ሾመው።

ቁጥር ፲፩ - ፳ ለማስተካከል

11፤በግብጽና፡በከነዓንም፡አገር፡ዅሉ፡ራብና፡ብዙ፡ጭንቅ፡መጣ፥አባቶቻችንም፡ምግብን፡አላገኙም። 12፤ያዕቆብም፡በግብጽ፡እኽል፡መኖሩን፡በሰማ፡ጊዜ፡በመዠመሪያ፡አባቶቻችንን፡ሰደዳቸው፤ 13፤በኹለተኛውም፡ዮሴፍ፡ለወንድሞቹ፡ታወቀ፥የዮሴፍም፡ትውልድ፡በፈርዖን፡ዘንድ፡ተገለጠ። 14፤ዮሴፍም፡አባቱን፡ያዕቆብንና፡ሰባ፡ዐምስት፡ነፍስ፡የነበረውን፡ቤተ፡ዘመድ፡ዅሉ፡ልኮ፡አስጠራ። 15፤ያዕቆብም፡ወደ፡ግብጽ፡ወረደ፥ርሱም፡ሞተ፥አባቶቻችንም፤ 16፤ወደ፡ሴኬምም፡አፍልሰው፡አብርሃም፡ከሴኬም፡አባት፡ከኤሞር፡ልጆች፡በብር፡በገዛው፡መቃብር፡ ቀበሯቸው። 17-18፤እግዚአብሔርም፡ለአብርሃም፡የማለለት፡የተስፋው፡ዘመን፡ሲቀርብ፥ዮሴፍን፡የማያውቀው፡ሌላ፡ጉሥ፡በግብጽ፡ላይ፡እስኪነሣ፡ድረስ፥ሕዝቡ፡እየተጨመሩ፡በግብጽ፡በዙ። 19፤ርሱም፡ወገናችንን፡ተተንኵሎ፡ሕፃናትን፡በሕይወት፡እንዳይጠብቁ፡ወደ፡ውጭ፡ይጥሉ፡ዘንድ፡አድርጎ፡ አባቶቻችንን፡አስጨነቀ። 20፤በዚያን፡ጊዜ፡ሙሴ፡ተወለደ፡በእግዚአብሔርም፡ፊት፡ያማረ፡ነበር፤በአባቱ፡ቤትም፡ሦስት፡ወር፡አደገ፤

ቁጥር ፳፩ - ፴ ለማስተካከል

21፤በተጣለም፡ጊዜ፡የፈርዖን፡ልጅ፡አነሣችው፡ልጅም፡ይኾናት፡ዘንድ፡አሳደገችው። 22፤ሙሴም፡የግብጾችን፡ጥበብ፡ዅሉ፡ተማረ፥በቃሉና፡በሥራውም፡የበረታ፡ኾነ። 23፤ነገር፡ግን፥አርባ፡ዓመት፡ሲሞላው፡ወንድሞቹን፡የእስራኤልን፡ልጆች፡ይጐበኝ፡ዘንድ፡በልቡ፡ዐሰበ። 24፤አንዱም፡ሲበደል፡አይቶ፡ረዳው፥የግብጽን፡ሰውም፡መቶ፟፡ለተገፋው፡ተበቀለ። 25፤ወንድሞቹም፡እግዚአብሔር፡በእጁ፡መዳንን፡እንዲሰጣቸው፡የሚያስተውሉ፡ይመስለው፡ነበር፥እነርሱ፡ ግን፡አላስተዋሉም። 26፤በማግስቱም፡ርስ፡በርሳቸው፡ሲጣሉ፡አገኛቸው፥ሊያስታርቃቸውም፡ወዶ፦ሰዎች፡ሆይ፥እናንተስ፡ወንድማማች፡ናችኹ፤ስለ፡ምን፡ርስ፡በርሳችኹ፡ትበዳደላላችኹ፧አላቸው። 27፤ያም፡ባልንጀራውን፡የሚበድል፡ግን፦አንተን፡በእኛ፡ላይ፡ሹምና፡ፈራጅ፡እንድትኾን፡የሾመኽ፡ማን፡ ነው፧ 28፤ወይስ፡ትናንትና፡የግብጹን፡ሰው፡እንደ፡ገደልኸው፡ልትገድለኝ፡ትወዳለኽን፧ብሎ፡ገፋው። 29፤ሙሴም፡ከዚህ፡ነገር፡የተነሣ፡ሸሽቶ፡በምድያም፡አገር፡መጻተኛ፡ኾኖ፡ኖረ፤በዚያም፡ኹለት፡ልጆች፡ ወለደ። 30፤አርባ፡ዓመትም፡ሲሞላ፡የጌታ፡መልአክ፡በሲና፡ተራራ፡ምድረ፡በዳ፡በቍጥቋጦ፡መካከል፡በእሳት፡ ነበልባል፡ታየው።

ቁጥር ፴፩ - ፵ ለማስተካከል

31-32፤ሙሴም፡አይቶ፡ባየው፡ተደነቀ፤ሊመለከትም፡ሲቀርብ፡የጌታ፡ቃል፦እኔ፡የአባቶችኽ፡አምላክ፣፡ የአብርሃም፡አምላክ፣የይሥሐቅም፡አምላክ፣የያዕቆብም፡አምላክ፡ነኝ፡ብሎ፡ወደ፡ርሱ፡መጣ።ሙሴም፡ ተንቀጥቅጦ፡ሊመለከት፡አልደፈረም 33፤ጌታም፦የቆምኽባት፡ስፍራ፡የተቀደሰች፡ምድር፡ናትና፥የእግርኽን፡ጫማ፡አውልቅ። 34፤በግብጽ፡ያሉትን፡የሕዝቤን፡መከራ፡ፈጽሜ፡አይቼ፡መቃተታቸውንም፡ሰምቼ፡ላድናቸው፡ ወረድኹ፤አኹንም፡ና፥ወደ፡ግብጽ፡እልክኻለኹ፡አለው። 35፤ሹምና፡ፈራጅ፡እንድትኾን፡የሾመኽ፡ማን፡ነው፧ብለው፡የካዱትን፥ይህን፡ሙሴን፡በቍጥቋጦው፡ በታየው፡በመልአኩ፡እጅ፡እግዚአብሔር፡ሹምና፡ቤዛ፡አድርጎ፡ላከው። 36፤ይህ፡ሰው፡በግብጽ፡ምድርና፡በቀይ፡ባሕር፡በምድረ፡በዳም፡አርባ፡ዓመት፡ድንቅና፡ምልክት፡እያደረገ፡ አወጣቸው። 37፤ይህ፡ሰው፡ለእስራኤል፡ልጆች፦እግዚአብሔር፡ከወንድሞቻችኹ፡እንደ፡እኔ፡ያለ፡ነቢይ፡ ያስነሣላችዃል፤ርሱን፡ስሙት፡ያላቸው፡ሙሴ፡ነው። 38፤ይህ፡ሰው፡በሲና፡ተራራ፡ከተናገረው፡መልአክና፡ከአባቶቻችን፡ጋራ፡በምድረ፡በዳ፡በማኅበሩ፡ውስጥ፡ የነበረው፡ነው፤ይሰጠንም፡ዘንድ፡ሕይወት፡ያላቸውን፡ቃላት፡ተቀበለ፤ 39፤ለርሱም፡አባቶቻችን፡ሊታዘዙት፡አልወደዱም፤ነገር፡ግን፥ገፉት፡በልባቸውም፡ወደ፡ግብጽ፡ተመለሱ፤ 40፤አሮንንም፦በፊታችን፡የሚኼዱ፡አማልክት፡ሥራልን፤ይህ፡ከግብጽ፡ምድር፡ያወጣን፡ሙሴ፡ምን፡እንደ፡ ኾነ፡አናውቅምና፡አሉት።

ቁጥር ፵፩ - ፶ ለማስተካከል

41፤በዚያም፡ወራት፡ጥጃ፡አደረጉ፡ለጣዖቱም፡መሥዋዕት፡አቀረቡ፥በእጃቸውም፡ሥራ፡ደስ፡አላቸው። 42፤እግዚአብሔር፡ግን፡ዘወር፡አለ፡የሰማይንም፡ጭፍራ፡ያመልኩ፡ዘንድ፡አሳልፎ፡ሰጣቸው፥በነቢያትም፡ መጽሐፍ።እናንተ፡የእስራኤል፡ቤት፥አርባ፡ዓመት፡በምድረ፡በዳ፡የታረደውን፡ከብትና፡መሥዋዕትን፡ አቀረባችኹልኝን፧ 43፤ትሰግዱላቸውም፡ዘንድ፡የሠራችዃቸውን፡ምስሎች፡እነርሱንም፡የሞሎክን፡ድንኳንና፡ሬምፉም፡የሚሉትን፡ የአምላካችኹን፡ኮከብ፡አነሣችኹ፤እኔም፡ከባቢሎን፡ወዲያ፡እሰዳችዃለኹ፡ተብሎ፡እንዲህ፡ተጽፏል። 44፤እንዳየው፡ምስል፡አድርጎ፡ይሠራት፡ዘንድ፡ሙሴን፡ተናግሮ፡እንዳዘዘው፥የምስክር፡ድንኳን፡ከአባቶቻችን፡ ዘንድ፡በምድረ፡በዳ፡ነበረች፤ 45፤አባቶቻችንም፡ደግሞ፡በተራ፡ተቀብለው፡እግዚአብሔር፡በፊታቸው፡ያወጣቸውን፡የአሕዛብን፡አገር፡ በያዙት፡ጊዜ፡ከኢያሱ፡ጋራ፡አገቧት፥እስከዳዊት፡ዘመንም፡ድረስ፡ኖረች። 46፤ርሱም፡በእግዚአብሔር፡ፊት፡ሞገስ፡አግኝቶ፡ለያዕቆብ፡አምላክ፡ማደሪያን፡ያገኝ፡ዘንድ፡ለመነ። 47፤ነገር፡ግን፥ሰሎሞን፡ቤት፡ሠራለት። 48-50፤ነገር፡ግን፥ነቢዩ፦ሰማይ፡ዙፋኔ፡ነው፥ምድርም፡የእግሬ፡መረገጫ፡ናት፤ለእኔ፡ምን፡ዐይነት፡ ቤት፡ትሠራላችኹ፧ይላል፡ጌታ፥ወይስ፡የማርፍበት፡ስፍራ፡ምንድር፡ነው፧ይህንስ፡ዅሉ፡እጄ፡የሠራችው፡ አይደለምን፧እንዳለ፥ልዑል፡የሰው፡እጅ፡በሠራችው፡አይኖርም።

ቁጥር ፶፩ - ፷ ለማስተካከል

51፤እናንተ፡ዐንገተ፡ደንዳናዎች፥ልባችኹና፡ዦሯችኹም፡ያልተገረዘ፥እናንተ፡ዅልጊዜ፡መንፈስ፡ቅዱስን፡ ትቃወማላችኹ፤አባቶቻችኹ፡እንደ፡ተቃወሙት፡እናንተ፡ደግሞ። 52-53፤ከነቢያትስ፡አባቶቻችኹ፡ያላሳደዱት፡ማን፡ነው፧የጻድቁንም፡መምጣት፡አስቀድሞ፡የተናገሩትን፡ ገደሏቸው፤በመላእክት፡ሥርዐት፡ሕግን፡ተቀብላችኹ፡ያልጠበቃችኹት፡እናንተም፡አኹን፡ርሱን፡አሳልፋችኹ፡ ሰጣችኹት፥ገደላችኹትም። 54፤ይህንም፡በሰሙ፡ጊዜ፡በልባቸው፡በጣም፡ተቈጡ፡ጥርሳቸውንም፡አፋጩበት። 55፤መንፈስ፡ቅዱስንም፡ተሞልቶ፡ወደ፡ሰማይ፡ትኵር፡ብሎ፡ሲመለከት፡የእግዚአብሔርን፡ክብር፡ኢየሱስንም፡ በእግዚአብሔር፡ቀኝ፡ቆሞ፡አየና፦ 56፤እንሆ፥ሰማያት፡ተከፍተው፡የሰው፡ልጅም፡በእግዚአብሔር፡ቀኝ፡ተቀምጥኦ አያለኹ፡አለ። 57፤በታላቅ፡ድምፅም፡እየጮኹ፡ዦሯቸውን፡ደፈኑ፥ባንድ፡ልብ፡ኾነውም፡ወደ፡ርሱ፡ሮጡ፥ 58፤ከከተማም፡ወደ፡ውጭ፡አውጥተው፡ወገሩት።ምስክሮችም፡ልብሳቸውን፡ሳውል፡በሚሉት፡ባንድ፡ጐበዝ፡ እግር፡አጠገብ፡አኖሩ። 59፤እስጢፋኖስም፦ጌታ፡ኢየሱስ፡ሆይ፥ነፍሴን፡ተቀበል፡ብሎ፡ሲጠራ፡ይወግሩት፡ነበር። 60፤ተንበርክኮም፦ጌታ፡ሆይ፥ይህን፡ኀጢአት፡አትቍጠርባቸው፡ብሎ፡በታላቅ፡ድምፅ፡ጮኸ።ይህንም፡ ብሎ፡አንቀላፋ።ሳውልም፡በርሱ፡መገደል፡ተስማምቶ፡ነበር።