ዙሪክ (Zürich) በስዊስ አገር የሚገኝ ከተማ ነው። በስዊትዘላንድ ከሁሉ ታላቁ ከተማ ነው። የከተማው ሕዝቡ ቁጥር 380,500 ሰዎች ሲሆን፣ በአካባቢው በጠቅላላ 2 ሚሊዮን ያሕል አሉ።

የዙሪክ ከተማ አርማ

ከተማው በሮሜ ሰዎች በ7 ዓ.ም. ሲመሠረት ስሙን ቱሪኩም አሉት። በ1520ዎቹ፣ የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ ማዕከል ሆነ። የፕሮቴስታንት ሰባኪ ኡልሪክ ዝቪንግሊ ከዙሪክ ነበረ።

ዙሪክ ከአለሙ ሁሉ አንደኛው ሀብታም ከተማ መሆኑ ይቆጠራል። የኗሪዎች ዋና መነጋገሪያ አለማንኛ ነው።