ዓለማየሁ ገላጋይ1960 ዓ.ም በአራት ኪሎ አካባቢ ተወለደ። በዳግማዊ ምኒልክ ፩ኛ ፪ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምሯል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስኩል ኦፍ ጆርናሊዝም ተምሮ ተመርቋል።

ዓለማየሁ ገላጋይ "ኔሽን" ፣ "አዲስ አድማስ" ፣ "ፍትሕ" ፣ "አዲስ ታይምስ" ፣ እና "ፋክት"ን ጨምሮ በተለያዩ ጋዜጦችና መጽሔቶች ላይ በሚያቀርባቸው መጣጥፎች ይታወቃል።

ሥራዎች

"ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ሕይወትና ክህሎት"፣ "ቅበላ"፣ "የብርሃን ፈለጎች"፣ "ኢህአዴግን እከሳለሁ"፣ "ኩርቢት"፣ "ወሪሳ"፣ "አጥቢያ"፣ "የፍልስፍና አፅናፍ"፣ "በፍቅር ስም"፣ "መለያየት ሞት ነው"፣ "በእውነት ስም (ታለ)"፣ "ውልብታ"፣ "በእምነት ሥም(ሐሰተኛው)"፣ "የተጠላው እንዳልተጠላ" የተሰኙ ልቦለድና ኢልቦለድ መፃሕፍት ለአንባቢያን አበርክቷል። ከዚህ በተጨማሪም "መልክዓ–ስብሐት" በተሰኘው መጽሐፍ 27 ጸሐፊያን፣ ደራሲያን፣ ገጣሚያንና ሰዓሊያን አሳትፎ በማሰናዳት ለአንባብያን አድርሷል።

ዓለማየሁ ገላጋይ በሃያሲነትም ስም ያተረፈ የብዕር ሰው ነው። ገና ለሕትመት ያልበቁ በርካታ ሥራዎችም አሉት።