• ፲፱፻፱ ዓ/ም - በግሪክ ሁለተኛ ከተማ በተሰሎንቄ (Thessaloniki) የተከሰተ የእሳት አደጋ የከተማዋን ቤቶች በቁጥር ከሦስት እጅ አንድ በማውደሙ እስከ ፸ሺ ነዋሪዎችን ውጭ አዳሪ ቤት አልባ አድርጓቸዋል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(International Olympic Committee - IOC) ዘረኛውን የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት ‘አፓርታይድ’ በሚል መርሆ የሚያካሂደውን የግፍ አስተዳደር እንዲያወግዝ ያቀረበለትን ጥሪ ባለመቀበሉ በዚህ ዓመት ቶክዮ ከተማ ላይ በተዘጋጀው ፲፰ኛው የኦሊምፒክ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ አገደው።