ዋሺንግተን ዲሲ
(ከዋሽንግተን ዲሲ የተዛወረ)
ዋሺንግተን ዲሲ (እንግሊዝኛ፦ Washington D.C.) የአሜሪካ ዋና ከተማ ነው። የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 570,898 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 38°55′ ሰሜን ኬክሮስ እና 77°00′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
የእንግሊዝ ሰዎች መጀመርያ በአካባቢው በደረሱ ወቅት (1600-1660 ዓ.ም.) በአሁኑ ዲሲ ሥፍራ ናኮችታንክ የተባለ የኗሪዎች ታላቅ መንደርና ንግድ ማዕከል ተገኘ። የአሁኑ ዋሺንግተን ከተማ የአሜሪካ አዲስ ልዩ ዋና ከተማ እንዲሆን በ1783 ዓ.ም. ተመሠረተ። በ1792 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት መቀመጫ በይፋ ከፊላዴልፊያ ወደ ዋሺንግተን ተዛወረ።
የከተማው ስም «ዋሺንተን» የአገሩን መጀመርያውን ፕሬዚዳንት ጆርጅ ዋሺንግተንን ያከብራል። «ዲሲ» (D.C.) ማለት በእንግሊዝኛ ለ«ዲስትሪክት ኦቭ ኮሎምቢያ» (District of Columbia ወይም የኮሎምቢያ ክልል) አጭር ነው።
ደግሞ ይዩEdit
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |