ካልቸር ኤንድ አርት ሶሳይቲ ኦፍ ኢትዮጵያ (እንግሊዝኛCulture and Art Society of Ethiopia) ባጭሩ ኬዝ (እንግሊዝኛ፦ CASE) በባህልና ጥበብ ሙያዎች ውስጥ ባሉ ሰዎች የተመሰረተ መንግሥታዊ ያልሆነ ማሕበር ነው።

የማሕበሩ ዓላማ የኢትዮጵያን ሰፊ የባሕልና የልዩ ልዩ ጥበባት ሃብት፣ የሕዝቦቿን ነባር ልማዶች፣ ሀገር በቀል ዕውቀት፣ አመለካከት፣ ማህበራዊ አስተዳደር፣ የተፈጥሮ ሀብትና ይህን ሃብት በመልካም ሁኔታ ለመጠበቅና ለመንከባከብ ያሏቸውን ጥበብና ዘዴዎች፣ በኣጠቃላይም የኢትዮጵያ ሕዝቦች የእኛ ናቸው የሚሏቸውን የእውቀት፣ የባሕልና የጥበብ ሀብት በመንከባከብ፣ በማልማትና ዘላቂነታቸው እንዳይደናቀፍ በማድረግ ረገድ ጠቃሚ የሆነ አስተዋፅኦ ለማበርከት ነው።