ኪነጥበብ ባትኖር አለም ጨው እንደሌለው ወጥ አልጫ ትሆን ነበር፡፡ የሰው ልጅም ከሌላ  ፍጡር ይቅርና ከመሰሉ ጋር ተዋዶና ተዛምዶ ለመኖር እጅጉን ይከብደው እንደነበር አያጠያይቅም፡፡ በዚህች አንዲት አለም ውስጥ እልፍ የሰው ልጆች መስተጋብር ፈጥረው የመኖራቸው ምስጢር ጥበብ እንደሆነች “ጥበብና አብሮነት” በሚል ርዕስ ሳንፎርድ ስኩል ኢኖቬሽን ሪቪው በገፀ-ድሩ ይፋ ባደረገው መረጃ አመላክቷል፡፡