እማሆይ ጽጌ ማርያም ገብሩ (ከምንኩስናቸው በፊት ይጠሩበት በነበረው ስማቸው የውብዳር ገብሩ) ታኅሣሥ 4 ቀን 1915 ዓ.ም. አዲስ አበባ ነበር የተወለዱት። ገና የስድስት ዓመት ሕጻን ሳሉ ከታላቅ እኅታቸው ከሥንዱ ገብሩ ጋር ወደ ስዊትዘርላንድ ሔደው “ሞንት ሚራል” በተባለ አካዳሚ ትምህርት ይጀምራሉ። በትምህርት ቤቱ ውስጥ ከቀለም ትምህርቱ በተጓዳኝ ቫየሊን እና ፒያኖ አጥንተዋል።[1]

የውብዳር ገብሩ 11 ዓመት ሲኾናቸው፣ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በዚህ ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወራ ነበር። ከንቲባ ገብሩም መላ ቤተሰባቸውን ይዘው ወደ ጎሬ ለመሠደድ ተገደዱ። የእኅቶቻቸው እና የእርሳቸው ትምህርት ተቋርጦ ከደስታ ገብሩ እና ከገነት ገብሩ ጋር በስደት ቆይተዋል።

እማሆይ ጽጌ ማርያም የጽሕፈት መኪና መምታት ተምረው ስለነበረ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ለጥቂት ጊዜ በጸሐፊነት ሠርተዋል። ሙዚቃን በከፍተኛ ደረጃ ለመማር ቁርጥ ውሳኔ ላይ የደረሱት ከዚህ ጊዜ በኋላ ነበር። ይህን ውሳኔያቸውን በማስታወሻቸው እንዲህ ሲሉ አስፍረውታል። “እንደገና አባባን አስቸግሬ፤ ጃንሆይን እንዲለምኑልኝ አስደርጌ ወደ ውጪ ሀገር ሔጄ የሙዚቃ ትምህርቴን እንድቀጥል ተፈቅዶልኝ ወደ ካይሮ ሔድኩኝ። ትካዜ እንደ ጓደኛ አይለየኝም ነበር። ብዙ የፍቅር መጻሕፍትን ስለማነብ ስለ ሰው ልጅ ጥሩ አስተሳሰብ አልነበረኝም። ሰው አታላይ ነው፣ ውሽታም ነው በማለት ሰውን እምብዛም አላምንም ነበር።” ይላሉ እማሆይ።

ለከፍተኛ የሙዚቃ ትምህርት ወደ ግብጽ ሔደው “ቬሉኑስ ኮንሰርቫቶሪ ኦፍ ሉቺኒያ” በተባለው የሙዚቃ ትምህርት ቤት አሌክሳንደር ኮንትሮቪች በተባለ ፖላንዳዊ የሙዚቃ መምህር ሥር ትምህርታቸውን ተከታትለዋል። አሌክሳንደር ኮንትሮቪች ኋላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ፤ በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትዕዛዝ የክብር ዘበኛ ሙዚቃን አደራጅቶ፤ በ1948 ዓ.ም. የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኦርኬስትራ ሙዚቀኞች በመምራት ከፍተኛ አስተዋጽዖ የነበረው የሙዚቃ ባለሙያ ነበር። እማሆይ ከትምህርታቸው በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው የሙዚቃ ቅማሬዎቻቸውን ማዘጋጀት ጀመሩ። “በዚህ ጊዜ ውስጥ” ይላሉ ወንድማቸው ኮ/ል ዳዊት ገብሩ። “በዚህ ጊዜ ውስጥ ከዕለታት አንድ ቀን የንጉሣዊ በተሰብ የኾኑ አንድ ሰው ለኹለት ዓመት ትምህርት ወደ እንግሊዝ እንድትሔድ የቅድሞሽ ቢከፍሉላትም፣ የይለፍ ወረቀቱን ኹሉ ይዛ ሳለ፣ ‘ከበላይ የመጨረሻ ፈቃድ አልተገኘም’ ተብላ ቀረች። ይህ ልክ በእኔ የደረሰብኝ ዓይነት ነው፤” ይላሉ ኮ/ል ዳዊት ገብሩ በመጽሐፋቸው። “አባቴ በ1922 ዓ.ም. …ለትምህርት ወደ ጀርመን ሊልኩኝ ቢያስቡም፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ሳህሌ ጸዳሉ ተመሳሳይ ዕግድ በማድረግ የትምህርት ዕድሌን አጨናግፈውብኛል። እኔ ብዙ ስላየሁ ቻልኩት እኅቴ ግን አልቻለችውም።” በማለት አጋጣሚውን በኀዘን ይገልፁታል።

በወጣትነታቸው በወሰኑት በዚህ የምንኩስና ሕይወት አባትታቸው እና እናታቸው ከፍተኛ ኀዘን ላይ ወደቁ። ብዙም አልቆዩ፤ እማሆይ በመነኮሱ በኹለት ዓመታቸው አባታቸው ከንቲባ ገብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ከዚያ በኋላ እማሆይ ሙሉ ጊዜያቸውን ለሙዚቃ ቅማሬ እና ለመንፈሳዊው ግልጋሎት ብቻ ወሰኑ። የመጀመሪያ ቅማሬያቸውን ለማስቀረጽ ወሰኑ። የዚህ ሙዚቃ የማስቀረጹ ውሳኔ፤ የራሱ የኾነ ምክንያት ነበረው። “ቅማሬዬን በሸክላ ለማስቀረጽ ያነሳሳኝ ዐቢይ ምክንያት ነበር። ጎንደር በነበርኩበት ጊዜ በየቤተክርስቲያኑ የማይጠገበውን ማኅሌት ሰምቼ ስመለስ፤ እደጅ የአገር ቤት ተማሪዎች በየሜዳው ጥቅልል ብለው ተኝተው አያለሁ። ብጠይቅ ሌሊት ቤተክስቲያን ያደሩ ናቸው፣ ጥግና ቤት የሌላቸው። በዚህም ልቤ ተነካ፣ አዘንኩ። እኔ ሀብት የለኝ፤ ያለችኝ ያቺው ሙዚቃዬ። ስለዚህ አስኪ ሙዚቃዬን ላስቀርጽ እና ሽያጩን እነዚህ ልጆች ገብተው በነጻ የሚያድሩበት ቤት ላቋቁም አልኩ። መከረኞቹም አሉ ሸክላውም ተቀረጸ። ነገር ግን ተንኮለኛ አይጠፋምና ለሽያጭ ከመቅረቡ በፊት እንጉሡ ጆሮ ስለ ደረሰ ሐሳቡ መና ቀረ መሞከሬ ግን አልቀረም።”

ይህንን በመሰለ “እርሳቸው ያልተረጋጋ” በሚሉት ሕይወት እስከ 1975 ዓ.ም. ከቆዩ በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሔዱ። እማሆይ በደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ከሦስት ዐሥርት ዓመታት በላይ ኖረዋል። ላለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት ስላሉበት ኹኔታ ምንም ዓይነት ዐዲስ ዜና ተሰምቶ ስለማይታወቅ በሕይወት መኖራቸውን የተጠራጠሩ ብዙዎች ነበሩ። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን፣ ሥራዎቻቸው የታላቅ ሙዚቀኞችን ቀልብ መሳብ ጀመረ። በወጣትነታቸው ብዙ መሥዋዕትነት የከፈሉለት፣ ማንም ልብ ሳይለው የዘሩት የረቂቅ ሙዚቃ የቅማሬ ዘር፤ ዛሬ ላይ ብዙዎች እርሳቸውን ብለው፣ የእርሳቸውን ሙዚቃ እንዲያጠኑ እያደረገ ነው።[2]

የዓለም ታላላቅ የዜና

የዓለም ታላላቅ የዜና አውታሮችም ከ2013 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ ስለ እማሆይ ሙዚቃዎች አዳዲስ ነገሮችን ማቅረብ ጀምረዋል። በ2013ቱ የኢየሩሳሌም የባህል ክብረ በዓል ከተከናወኑ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በእማሆይ ሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ሥራዎች ዙሪያ ያተኮሩ ተግባራት ነበሩ። ባለኹለት ጥራዝ መጻሕፍትን በእማሆይ የሕይወት እና የሙዚቃ ሥራዎች ላይ መታተም ችለዋል። የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን በኖታ የያዘ ባለ 146 ገጽ መጽሐፍም ታትሟል። እንደ ናዳቭ ሀርፐር ያሉ የእስራኤል ታላላቅ ሙዚቀኞች ስለ እማሆይ ሥራዎች ጥልቀት ምስክርነት እየተሰጡ ይገኛሉ።

በወጣትነት ዕድሜ የተሠራ የአስተውሎት ሥራ የኋላ ኋላ የራሱ ትንሣኤ ይኖረዋል። የእማሆይ ጽጌ ማርያም ሕይወት በሙዚቃ በብዙ ተፈትነዋል። ከመንፈሳዊ ሕይታቸው ጋር የሚቃረን የሚመስላቸው አንዳንዶች፣ ሙያቸውን እና የሙዚቃ ፍቅራቸውን አጣጥለውባቸዋል። የሕይወታቸውን አቅጣጫ ፍጹም በማይገመት መንገድ እንዲጓዝ ያደረገም ነው። ከሀገራቸው አሰድዶ በሌላ በዓት ተነጥለው እንዲኖሩ ያደረገ ነው። ግን ከዚህ ኹሉ በኋላ የስማቸውን ትንሣኤ ዕድለኛ ኾነው፣ ከዘጠኝ ዐሥርት ዓመታት በኋላ በታላቅ ክብር ከብዙዎች ብድራቱን አግኝተውበታል። በቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር ቤት ከንጉሠ ነገሥቱ ብቻ በቀር ማንም በትዕግሥት ሊያዳምጠው ያልቻለው ኮንሠርታቸው፤ ሐምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ሥራዎቻቸውን በሚጫወቱ ወጣቶች አማካኝነት ከ1800 በላይታዳሚያን በተገኙበት በአድናቆት ተመልካች አግኝቷል። ገና ያልተደመጡት አዳዲሶቹ ስድስት ክላሲካል ቅማሬዎቻቸው በትልቅ ኦርኬስትራ ሊቀርቡ ዝግጅት እየተደረገ ነው።

ውልደት እና እድገት ለማስተካከል

የውብዳር ገብሩ 11 ዓመት ሲኾናቸው፣ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ። በዚህ ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወራ ነበር። ከንቲባ ገብሩም መላ ቤተሰባቸውን ይዘው ወደ ጎሬ ለመሠደድ ተገደዱ። የእኅቶቻቸው እና የእርሳቸው ትምህርት ተቋርጦ ከደስታ ገብሩ እና ከገነት ገብሩ ጋር በስደት ቆይተዋል።

ምንኩስና ለማስተካከል

ዚህ በኋላ የወጣቷ፣ በሙዚቃ ብዙ የመግፋት ጉጉት የነበራት የየውብዳር ገብሩ የሕይወት መስመር ሌላ አቅጣጫ ያዘ። የዚህ ዕድል መሰናከል ምን እንዳስከተለ የእማሆይ ማስታወሻ እንዲህ ይገልፀዋል።“የመጨረሻ ዕድሌ በመሰበሩ፣ መንፈሴ ተሰባብሮ፣ ሞትን ብቻ ፈለግኹ። ከ15 ቀን በላይ እህል ውኃ ሳልቀምስ ጥቁር ባዶ ቡና ብቻ እየጠጣሁ ስሰነብት፤ ያው የሞት ጥላ በላዬ ላይ ሲያንዣብብ፣ የመጨረሻ ቁርባን እንዲሰጠኝ ጠይቄ አንድ ቄስ እስከነበርኩበት ምስካየ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም አጠገብ እነበረው ሆስፒታል ድረስ መጥተው አቆረቡኝ። የዚህ ዓለም ፍቅር እና የመኖር ፍላጎት ከኅሊናዬ  ፈጽሞ ተወገደ፤” ይላሉ።

በቤተሰቦቻቸው ርብርብ ሕይወታቸው

በቤተሰቦቻቸው ርብርብ ሕይወታቸው ተርፎ ጥቂት የተጽናኑት እማሆይ፤ ቤተሰቦቻቸውን አዘናግተው ወደ ግሼን ደብረከርቤ ተጓዙ። “ለኹለት ዓመታት አንድ ቀን ሳይቋረጥብኝ ሰዓታቱንም፣ ቅዳሴውንም ሥራውንም ከዘለቅሁት በኋላ ስቆረጠልኝ። የኹለት ወር ፈቃድ እና ደመወዝ ይዤ ከአንድ ዓመት በፊት ከእናቴ ከወ/ሮ ካሣዬ ጋር ሔጄበት ወደነበረው ወደ ግሼን ማርያም ተጓዝኩ። ወደዚያ ስሔድ ግን ነፋስ መለወጥ አለብኝ ብዬ አባባን እና እናቴን አስፈቅጄ ነው። እነርሱ ምንም አልጠረጠሩም ነበረና ለሽርሽር የምሄድ መስሏቸው ፈቀዱልኝ።” ይላሉ። ከዚያም ለግሼኑ አቡነ ሚካኤል መመንኮስ እንደሚፈልጉ ይነግሯቸዋል። “ዘመዶችሽ በኋላ መጥተው ቢያስቸግሩስ?” ቢሏቸው፤ “በነፍሴ የሚያዝባት ሰው ካለ እኔ ሌላ የለም።” ስላሉዋቸው ምንኩስናው ተፈቀደላቸው። ከምንኩስናው በፊት በጸጉር የመላጨቱ ሥነ ሥርዓት ወቅት የተከሰተው ነገር እዚህ ላይ ሳይጠቀስ አይታለፍም። “ከእንክብካቤ እቅፍ ውስጥ ወጥቶ ተሞነጫጭሮ ትከሻዬ ላይ የተዘረገፈውን ፀጉሬን ዐይተው አቡነ ሚካኤል፤ ‘ይህ ጠጉር ደግሞ መላጨት አለበት፤ ’ አሉኝ። ቀጠል አድርጌ ኧረ እርሱስ ግድ የለም አልኳቸውና አባ ደሳለኝ የሚባሉትን የደሴ ግቢ መርቆርዮስ አስተዳዳሪ እንዲላጩኝ ጠየቅኳቸው። አባ ደሳለኝ ሲላጩኝ እጃቸው ለብዙ ጊዜ ሲያርፍ ‘ምን ኾነው ነው?’ ብዬ ዘወር ብዬ ሳያቸው፤ ዕንባ አውጥተው ሲያለቅሱ ዐየሁና ‘ምነው አባቴ ምን ኾኑ?’  ብላቸው፤ ‘አባቴ እንኳን ሲሞት አላለቀስኩም፣ እንዲያው አዝኜ ነው’ አሉኝ። እኔም ‘ምን ለፀጉሩ ነው ይህንን ያህል የሚያዝኑት’ ብዬ ቀለድኩባቸው። እንኳንስ ፀጉር ሌላም በነበረኝ ለጌታዬ የምሰጠው አልኳቸው።” ይላሉ። በዚህ ዕለት ማግስት የምንኩስና ሥርዓቱ ተፈጸመላቸው። ይህ ሲኾን ዕድሜያቸው 20ዎቹ መጀመሪያ ላይ ነበር።

ሙዚቃ ለማስተካከል

የዓለም ታላላቅ የዜና አውታሮችም ከ2013 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ ስለ እማሆይ ሙዚቃዎች አዳዲስ ነገሮችን ማቅረብ ጀምረዋል። በ2013ቱ የኢየሩሳሌም የባህል ክብረ በዓል ከተከናወኑ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በእማሆይ ሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ሥራዎች ዙሪያ ያተኮሩ ተግባራት ነበሩ። ባለኹለት ጥራዝ መጻሕፍትን በእማሆይ የሕይወት እና የሙዚቃ ሥራዎች ላይ መታተም ችለዋል። የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን በኖታ የያዘ ባለ 146 ገጽ መጽሐፍም ታትሟል። እንደ ናዳቭ ሀርፐር ያሉ የእስራኤል ታላላቅ ሙዚቀኞች ስለ እማሆይ ሥራዎች ጥልቀት ምስክርነት እየተሰጡ ይገኛሉ።

መታሰቢያ ለማስተካከል

የእማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ ህልፈትን ተከትሎ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ "ዝክረ እማሆይ ጽጌማርያም ገብሩ" የተሰኘ የመታሰቢያ መረሃ ግብር በቀጣዩ 15 ቀናት ውስጥ እንደሚዘጋጅ መምህር ዕዝራ አባተ ለቢቢሲ ገልጸዋል።[3]

በዚህ የመታሰቢያ መረሃ ግብር ላይ "በተቻለ መጠን እማሆይን ጽጌማሪያም የሚያስታውስ መሰናዶ በያሬድ ሙዚቃ ትምህር ቤት ይከናወናል" ብለዋል መምህሩ።

ይህ መሰናዶ "ወጣቶች እንዲያስታውሷቸው" ያለመ እንደሆነ ዕዝራ ተናግረዋል።

አያይዘው እንደገለጹት የመሰናዶው ዋነኛ ይዘት የእማሆይ ጽጌማርያም ሙዚቃዊ አበርክቶ ይሆናል።

"በዋነኛነት ትምህርታዊ አበርክቷቸው ላይ የሚያተኩር ይሆናል። በኢትዮጵያ ሙዚቃ ያላቸውን አስተዋጽኦም ይዳስሳል" ሲሉ አስረድተዋል።

በዚህ የመታሰቢያ መረሃ ግብር ላይ ሙዚቀኞች እንዲሁም መምህራን ይሳተፉበታል ተብሎ እንደሚጠበቅም መምህር ዕዝራ አባተ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

ታዋቂ ስራዎች ለማስተካከል

ማያ ከእማሆይ አሳዛኝ ቅንብሮቻቸውን እንደምትወድ ብሎም ሦስቱን ለይታ እንደምትወዳቸው ትናገራለች።

"በእርግጥ ይሄ አሁን ላይ ያለ እንጂ እንደጊዜው፣ እንደ አየር ሁኔታው እና እንደ ስሜቴ ሊቀያየር ይችላል (ሳቅ)" ትላለች ማያ።

ዘ ጋርዲያንስ ኦፍ ጌትሰማኔ፣ ጎልጎታ እና ጄሩሳሌም አሁን ላይ የምትወዳቸው እና የምታዳምጣቸው የእማሆይ ቅንብሮች ናቸው።

"ዘ ጋርዲያንስ ኦፍ ጌትሰማኔ በሕብረ ቀለማት የተንቆጠቆጠ፣ ኮርድስ እና ፎልስ ሩር ኤግዞቲክ ፍላወር። [4]

  1. ^ https://abiy.wordpress.com/2023/03/30/%E1%8A%A5%E1%88%9B%E1%88%86%E1%8B%AD-%E1%8C%BD%E1%8C%8C-%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%9D-%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A9-%E1%8A%A81915-2015-%E1%8B%93-%E1%88%9D/
  2. ^ https://www.emahoymusicpublisher.com/about-emahoy
  3. ^ https://www.bbc.com/amharic/news-60741168
  4. ^ http://www.tadias.com/03/27/2023/pianist-composer-emahoy-tsegue-maryam-guebrou-passes-away-at-age-99/