ኣበቃ ወይም ምስርች (Rotheca myricoides) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

አበቃ

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ ለማስተካከል

ብዙ ጊዘ ከአንድ ሜትር በላይ ይደርሳል፣ ሰማያዊ፣ ወይን ጠጅ ወይም ነጭ አበቦች አሉት።

አስተዳደግ ለማስተካከል

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር ለማስተካከል

በቆዩ መኖርያ ቤቶችና በተፈጁ ኮረብቶች በጣም ተራ ነው።

በመጀመርያ ከአፍሪካ ሲሆን በሌላ አገር እንደ አበባ ይታደጋል።

የተክሉ ጥቅም ለማስተካከል

ሥሮቹን በማፍላት የተሠራው መረቅ መርዝን የሚሽር መድኃኒት በመሆን ይጠጣል።

እንዲሁም ተክሉ ትልን ለመግደል፣ በከብትም ለሚያስቀምጥ መድኃኒት ተጠቅሞዋል። የተክሉ መረቅ ደግሞ ለቁስል ፋሻ ይጠቀማል።

ብሳና ቡቃያና ከእምቧይ ሥር ጋራ ተቀላቅሎ፣ የሆድ ድርቀት ለማከም በአፍ ይወሰዳል። ቅቤም ለለጥፉ ይጨመራል።[1]

ደብረ ሊባኖስ ዙሪያ እንደ ተዘገበ፣ «አልማዝ ባለጭራ የሚባል ልክፈት ለማከም የምስርች ቅጠል ተድቅቆ በውሃ ይለጠፋል።[2]

ፍቼ ወረዳ እንደ ተዘገበ፣ የምስርች ሥር ጭማቂ በውሃ ለማስታወክ ይጠጣል።[3]

  1. ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ በደብረ ሊባኖስ ዙሪያ ያለው ሕዝብ መድሃኒታዊ እጾች እውቀናና ጥቅም 1998 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ ግርማይ መድኅን፣ ያለም መኮነን፣ አዲስ አበባ ዩኒቬርሲቴ፣ አክሊሉ ለማ ተቋም
  3. ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች