ዉቃቢ የሚለዉ ቃል አቃቢ ለወንድ አቃቢት ለሴት ከሚል የግእዝ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም "ከልካይ" "ጠባቂ" "ዘብ" ማለት ነው። ይህ ቃል እንደስም ሆኖ በሰዉ ላይ ለሚናገር የቅዱሳን መላእክት መንፈስ ያገለልላል። በኢትዮጵያም የአብዛኛዉ ህዝብ እምነት ሲሆን ከኦሪት የአምልኮ ስርአት ጋር የተያያዘ መልክ አለዉ። በታሪክ ዉርርስ ብቻ የተላለፈ እምነት ነዉ። ከራማ፤ ቃሉ፤ አወልያ፤ ቆሌ፤ የአባት እና የእናት-አምላክ የሚሉ መጠሪያዎችም ተለምዶአዊ ስሞች ናቸዉ። በኢትዮጵያ የባህል እምነት አምልኮ ዉስጥ ወሳኝ የእምነቱ አስፈጻሚ ነው።በተዋቀረ ስርአት የኦሮሞ ህዝብ ዋቄፈና ብሎ ያከብረዋል።