ነዪ ብዪ እንጂ

(59)ጾም ነው ሮቡዕ ቀን። አለቃ ጸሎት ከአጥር ግንብ ጎን ሆነው ይደግማሉ እንደገናም ወዴቤት እያሾለቁ ይመለከታሉ። ወይዘሮ ማዘንጊያ ወተት ንጠው ወተቱን አፍልተው አይብ ሠርተው እሱን ጎረስ ጎረስ ጎረስ በጤፍ እንጀራ ያደርጋሉ። አለቃ ይኼንን አይተዋል። ፀሎት አሣርገውወደ ቤት ይገባሉ ከሠዓት ላይ ነው። ለአለቃ ማዘንጊያ ቁርስም ምሣቸውን በማሰብ ምግብ በሽሮ ወጥ ያቀርቡላቸዋል። ይሔኔ አለቃ ማዘንጊያሽ «ነይ ብዪ እንጂ» ይሏቸዋል። ማዘንጊያም «አለቃ ምግብ አልበላ ብሎኛል ይሏቸዋል» ይሄኔ አለቃ «አንቺ ባይበላሽ እኔ እበላዋለሁ» ብለው ብቻቸውን ምሣቸውን በሉ ይባላል።