ደጃዝማች ኃይለማርያም ማሞ ስመ–ጥር አርበኛ ነበሩ። ከ 1928 እስከ 1933 በነበሩት የትግል ዓመታት አገራቸውን ከጣሊያን ወራሪ ጦር ለመከላከል ዘመቱ። ኃይለማርያም ማሞ በጀግንነትና በቆራጥነት በመዋጋት ድፍረትን የተላበሱ ወኔኛ አርበኛ እንደነበሩ ይነገርላቸዋል። ጦርን በማደራጀትና ለውጊያ በማሰለፍ የላቀ ችሎታ እንደነበራቸው ይወሳል። ደጃዝማች ኃይለማርያም ከሚመሰገኑበት የጦር ሜዳ ውሎ አንዱ ከቆሰሉ በኋላ እንኳ በውጊያ የመቀጠላቸውና ጠላትን ቁም ስቅል የመንሳታቸው ጉዳይ ነው።