Bonanza (ቦናንዛ) ከ1959 እስከ 1973 እ.ኤ.አ. ድረስ የተሠራ አሜሪካዊ ትርዒት ነበር። የካርትራይት ቤተሠብ፣ ቤንጃሚን ካርትራይት እና ሦስት ልጆቹ «ፖንዴሮሳ» በሚባል ሠፈር ላይ ታሖ ሐይቅ አጠገብ በኔቫዳ ግዛት 1860ዎቹ ይኖራሉ።ጎረቤቶቻቸው የፓዩት ኗሪ ጎሣ እና የብር እና ወርቅ ፈላጊዎች ከተማ ቪርጂንያ ሲቲ ናቸው። በዚህ አለም ሰው ከሌላ ሠፈር የደረሰ እንደ ሆነ የመንጋ ሌባ ሊሆን ይችላል።የመንጋ ሌቦችም ሆነ በር እና ወርቅ ፈላጊዎች አለግባብ በፖንደሮሳ ሲገቡ ግን፣ ካርትራይቶቹ በፈረስ ላይ ሁነው ያባሯቸዋል።

የካርትራይት ቤተሠብ

የካርትራይት ቤተሠብ እና ርስታቸው ፖንደሮሳ ልብ ወለድ ቢሆኑም፣ ዕውነተኛ ታሪካዊ ሰዎች ደግሞ አንዳንዴ ይታዩበታል፣ ለምሳሌ ማርክ ትዌንሄንሪ ኮምስቶክ፣ እና የፓዩት አለቃ ውነሙካ።«ቦናንዛ» ማለት የማዕድን ፈላጊዎች ሞልቶ የተትረፈፈ ማዕድን ባገኙ ግዜ፣ «ቦናንዛ» ይሉት ነበር።