ሺ ነዋ

(47)አለቃ ገብረሃና አጤ ምኒልክ ግብር ሊበሉ ሄዱ። ተበልቶ ተጠጥቶ ለሽንት መውጣት አይፈቀድም ነበር። አለቃ ግን እወጣለሁ ብለው ተወራረዱ። ዘበኞች አናስወጣም ቢሏቸው «እምዬ ምኒልክ ለሽንት እንድወጣ ፈቅደውልኛል አሉ።» ዘበኞቹ «አይደረግም አሉ።» አለቃ «በሉ ንጉሱ ምን እንደሚሉ ስሙ አሉዋቸው።» ወደእምዬ ምኒልክ ጠጋ ብለው በጆሮዋቸው አንሾካሸኩ። «"500+500" ስንት ይሆናል?” እምዬ ምኒሊክም ሂሳብ አይችሉም እንዳይባሉ ጮክ ብለው «ሺነዋ» አሉ። አለቃም «ሺነዋ (ሽናው ) ተብዬአለሁ» ብለው ወደሽንት ቤት ሄዱ።