ስላንቺኢትዮጵያ አስቂኝ የፍቅር ፊልም ነው። ፊልሙ በኢትዮጵያ ሲኒማ ቤቶች ረዥም ጊዜ የቆየ ሲሆን በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቷል። በ4ኛው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል 3 ሽልማቶችን ያገኘ ሲሆን በኒው ዮርክ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ላይም በተመሳሳይ ምርጥ ዓለም አቀፍ አስቂኝ የፍቅር ፊልም ተብሎ ተሸልሟል።