ሲዳማ

ሲዳማ የኢትዮጵያ ብሔር ነው። ሲዳማ


ሲዳማ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብሄሮች አንዱ ሲሆን በህገመንግሥቱ ከተቀመጠው የብሄር ብሄረሰቦች መብት አንፃር በእጅጉ የተጠቀመ ብሔር ነው፡፡ጠቀሜታው ባለፉት 29 ዓመታት ደቡብ ክልል ከመሩ 6 አስተዳዳሪዎች አምስቱ ሲዳማ መሆናቸው ነው አባተ ኪሾ፤ ሽፈራው ሽጉጤ ፤ ደሴ ደልኬ ፤እና ሚሊዮን ማቴዎስ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሲዳማ በህዝብ ቁጥር 10 ሚሊዮን ሲሆን በዞን ደረጃ እንዲተዳደር የህወሓት ማፊያዎች የሀገሪቱ ሁለት ታላላቅ የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦችን ለመጨቆን ህወሓት ካለው የትግራይ 1.8 ሚ ህዝብ(በሗላ የዓማራውን መሬትና ህዝብ ከዘረፉ በሗላ 4ሚ ሞልተናል ብለዋል) . . ከደቡብ "ጥቃቅንና አነስተኛ" ብሐረሰቦች ጋር ሲዳማን በመጨመር "አሻንጉሊት" የሆነ ደኢህዴን የሚባል ድርጅት(የፖለቲካ ፓርቲ ያልሆነ ) ለህወሀት መጠቀሚያ ተራ የሆዳም ስብስብ በመመስረት አማራና ኦሮሞዎችን ለማፈን የግድ ሲዳማን ማፈን ምርጫ በመሆኑ ነበር፡፡

የሲዳማ ሕዝብ የሚኖረው በደቡብ ኢትዮጵያ በሲዳሞ ክፍል ሀገር ሲሆን በሰሜን ከሸዋ ፤ በሰሜን ምስራቅ ከአርሲ በምስራቅ ከባሌ፤ በደቡብ ምሥራቅ ከጀምጀም በደቡብ ከጌዲኦ ጋር ይዋሰናል፤ በምዕራብ በኩል ከወላይታ የሚያዋስነው የብላቴ ወንዝ ሲሆን በሰሜን ምዕራብ የአዋሳ ሀይቅ እና በደቡብ ምዕራብ የአባያ ሀይቅ ያዋስኑታል፤

የሲዳማ አውራጃ ከባሕር ወለል በላይ 4500 - 10 000 ጫማ ከፍታ ያላት ናት፤ ስለሆነም ከፍታው እንደሚጠቁመው አብዛኛው ክፍል ወይና ደጋ ቢሆንም ደጋ እና ቆላማ ይገኙበታል፤ በዚህም መሠረት ከ 8-10 ሺህ ጫማ ከፍታ ያለው አካባቢ ወደ ደጋው ክፍል ይቆጠራል፤ በዚህ ክፍል ውስጥ የገረንባ ፕላቶ እንደ ምሳሌ ሆኖ ሊቀርብ ይችላላ፤ የገረንባ ፕላቶ ከሰሜን ምስራቅ አዋሳ ወረዳ ይነሳ እና እንደ ሰንሰለት በመያያዝ የሸበዲኖን የዳሌን ወረዳዎች የምስራቃዊውን ጫፍ እየቆራረጠ ሲሄድ፤ የአርቤጎናን ምዕራብ ክፍል እያቀፈ ይሄድ እና የሀገረ ሰላምን ወረዳ አብዛኛውን ክፍል ይዞ ከአለታ ወንዶ ወረዳ እየለየ ሲሄድ እስከ ጌዲኦ አውራጃ ይደርሳል፤ ይሄው ፕላቶ በአንዳአንድ ቦታዎች ከፍታው በግምት ከባህ ጠለል እስከ 10 ሺህ ጫማ ይደርሳል፤፤ ፕላቶው የባሌ ማሲፍ አካል መሆኑ ነው፤ ከገረንባ ፕላቶ በሁለቱም በኩል የሚመነጨው ብዙ ወንዞች እና ጅረቶች አሉ፤ ከኮረብታው በስተምዕራብ ከሚመነጨው ወንዞች መካከል ኮላ እና ጊዳዋ ወደ አባያ ሀይቅ እና ከከገረንባ በስተምስራቅ ከሚመነጩት መካከል ኤሬርቱ፤ ገላና እና ሎግታ ዋና ዋናዎች ናቸው፤ የሎግታ ወንዝ ትልቅ ፎፋቴ ያለው ከመሆኑ በላይ ገላና ኤሬርቱ ቦሮናን እያስከተለ ይሄድ እና እና ከጋምቤልቱ ወንዝ ጋር ከተቀላቀለ በሆላ ትልቁ የገናሌ ወንዝ ይሆናል፤ ወይና ደጋው ከሁሉ ስፋት ያለው ሲሆን፤ ከ5500 ጫማ በታች ከፍታ ያለው አካባቢ ወደ ቆላው ይመደባል፤ ከአባያ ሐይቅ አንስቶ የብላቴን ሸለቆ ይዞ እስከ ሐዋሳ ሀይቅ ድረስ በዚህ ክፍል ውስጥ ይመደባል፤ [1]

አሁን ደግሞ ክብር ለብልጽግና ፖርት ሆኖ የ130 ዓመት ጥያቄ ተመልሶ ስዳማ የኢትዮጵያ 10ኛዉ ክልል ሆኗል። [1]

  1. ^ ከቤተና ሆጤሳ; ሲዳማ ህዝብ እና ባህሉ ፤