ሥነ ዲበ አካል ማለት ኅልውና ያላቸው ማናቸውም ነገሮች የበላይ ጥናት ማለትነው። ዲበ አካል የሚለው ቃል ከሁለት ቃላት የመጣ ነው። ዲበ ማለት፣ በላይ ወይን ባሻገር ያለ ማለት ነው። አካል ማለት ተጨባጭ ማለት ነው። ሥለሆነም ዲበ አካል ማለት ከተጨባጩ ዓለም ባሻገርና በስተጀርባ ያለ ረቂቅ ነገር ማለት ነው። ሥነ ኑባሬ የዚህ ጥና ክፍል ነው።