ምዝ ፓክ-ማን ከ1973 ዓም ጀምሮ የወጣ ቪዴዮ ጌም አርኬድ ጨዋታ ሆኗል። በአለም በተለይም በስሜን አሜሪካ ከ1973-1977 ዓም ለወጣቶች እጅግ ዘመናዊ የባሕል ተጽእኖ አደረገ። ጨዋታው እንደ ፊተኛው ፓክ-ማን ቢመስልም፣ በተለያዩ ረገዶች በጣም የተሻለ አጨዋወት አቀረበ። በነዚህ ዓመታት ብዙ ሌሎች አርኬድ ጌሞች ቢወጡም ምንጊዜም ይህንን ጌም የመረጡ ይገኙ ነበር። ከ1980 ዓም ያህል በኋላ ሰዎች እቤታቸው ውስጥ ቪዴዮ ጌም ይጫወቱ ስለ ነበር ትልቁ የአርኬድ ባሕል ተጽእኖ ይቀነስ ጀመር።

የምዝ ፓክ-ማን ጨዋታ 1973 ዓም