ሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ ሃ/እየሱስ በ1922 ዓ.ም. የካቲት 29 ከእናታቸው ከወ/ሮ ይመኙሻል እና ከአባታቸው ከመምሬ ሃ/እየሱስ ሃ/ስላሴ ተወለዱ። ሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ በየካ ሚካኤል ቤተ ክርስትያን በዋና ቀዳሽነት ያገለገሉ እና በ1954 ዓ.ም. የየካ ሚካኤል ሰንበቴ ቤት መሥራች የነበሩ ናቸው። የሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ ባለቤት ወ/ሮ ፅጌ ገ/ፃድቅ ይሰኛሉ። ሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ ከባለቤታቸው ጋር ዘጠኝ ልጆችን አፍረተዋል። መኖሪያ ቤታቸውም በመገናኛ የካ ተራራ በተለምዶ ደረጃ ሰፈር ተብሎ የሚጠራው መንደር አካባቢ ነው። ሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ በህይወታቸው ብዙ ውጣውረድን ያሳለፉ ሰው ናቸው። እናም የብዙ አርቲስቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ንስሀ አባት ነበሩ። ከንስሀ ልጆቻቸውም መካከል አርቲስት ዘለቀ ገሠሠ ፣ የኮሎኔል መንግስቱ ኀ/ማርያም አባት አቶ ኀ/ማርያም ጥቂቶቹ ናቸው። ሊቀ ትጉኀን መምሬ ከበደ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት 2008 ዓ.ም. ጷግሜን 4 ቀን ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ቀብራቸውም በየካ ሚካኤል ሰንበቴ ቤት ተፈፀመ።