መላኩ ወረደ ለማስተካከል

ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ከኣሉ ስምንት የተለያዩ የእጽዋት ክምችቶች ከኣሉበት ኣገሮች ኣንዷ ናት። ኢትዮጵያ ላይ በተደጋጋሚ በደረሰው ድርቅና ጠኔ የተነሳ የኣገርዋ የሰብል ዘሬች እንዳይጠፉ በመሰብሰብና እንዳስፈላጊነቱም መልሶ ለገበሬዎች በመስጠት ዶ/ር መላኩ ወረደ የሚደነቅ ሥራ ኣከናውነዋል። የሥራቸውም ውጤት ከኣፍሪቃ ተርፎ በዓለም ከኣሉት ኣስተማማኝ ክምችቶች ኣንዱ ሆኗል። ዶ/ር መላኩ በእርሻ ማልማት ላይ የብዙኅ ሕይወትን ለመጠበቅና ለማብዛት እንደሚቻል ያሳወቁ፣ ያረጋገጡ ፈር ቀዳጅ ተመራማሪ ስለመሆናቸውም ዓለም አቀፍ ዘገባዎች ይመሰክራሉ።

ዶ/ር መላኩ ወረደ ይህ የእጽዋት ክምችት እንዳይጠፋ በኣለፉት ኣያሌ ዓመታት ትልቅ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል። ለእዚህም ሥራቸው “ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ” ወይም “Right Livelihood Award” የሚባል ሽልማት በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ተሰጥቷቸዋል።

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል