መላኩ ተፈራ ደርግኃይለስላሴን አገዛዝ ገርስሦ ስልጣን በያዘ ጊዜ በጎንደር አከባቢ ለአብዮቱ አልታዘዛችሁም በማለት ብዙ ሺ ወጣቶችን በመረሸንና በማስረሸኑ በጭካኔው ይታወቃል። በመሆኑም የጎንደር እናቶች እንዲህ ሲሉ አዚመውለታል። <<መላኩ ተፈራ የእግዜር ታናሽ ወንድም የዛሬውን ማረኝ እንጂ ሌላ ልጅ አልወልድም>> መቶ አለቃ መላኩ ተፈራ ለሰራው እጅግ አሰቃቂ የግድያ ወንጀሎች አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ ፈርዶበታል።