ሒስ (እንግሊዝኛ፦ ክሪቲሲዝም criticism) ማለት የአንዱን ነገር ወይም አካሄድ ዋጋ ወይም ጉድለት መተቸት ወይም ማመልከት ነው።

ሓያሲ በእንግሊዝኛው አጠራር "ክሪቲክ" critic በመባል የሚታወቀው ሐሳብ ገባሪውንም ያመለክታል። በአማርኛ ሒስ የግብሩ፣ ሐያሲ ደግሞ የገባሪው መጠሪያ ሆኖ ያገለግላል ። ግብሩ ግምገማ፣ ግምት፣ ፍርድ፤ ገባሪው ደግሞ ገምጋሚ፣ ገማች፣ ፈራጅ ማለት ነው።