ከ«ሚስቶች በኖህ መርከብ ላይ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
ከ[[ማየ አይህ]] በፊት በነበሩ ዕለታት ስለ ኖሩ በ[[ኖህ]] መርከብ ላይ ስለ ተገኙ ስለ አራቱ ሴቶች [[ኦሪት ዘፍጥረት]] ምንም እንኳን ዝም ቢል፣ ከሌላ ምንጭ ስለነዚሁ ሴቶችና በተለይ ስለ ስሞቻቸው የተገኘው [[አፈ ታሪክ]] በርካታ ነው።
 
በጥንታውያን እምነት ዘንድ፣ የ[[ሴም]]፣ የ[[ካም]]ና የ[[ያፌት]] ሚስቶች ዕጅግ የረዘማቸው ዕድሜ ሲኖራቸው ከመጠን ይልቅ ለብዙ መቶ ዓመታት ኑረው ለያንዳንዱ ትውልድ ትንቢት እየተናገሩ ኖሩ። እነኚህ [[ሲቡሎችሲቢሎች]] ተብለው ለ[[ግሪኮች]] ለ[[ሮማውያን]]ም እንደ ቅዱሳን መጻሕፍት የተቆጠሩት [[ሲቡላውያንየሲቢሊን መጻሕፍት]] ደራሲዎች እንደ ነበሩ ታመነ። የሮማውያን ቅጂ በ[[397]] ዓ.ም. አካባቢ በእሳት ተቃጥሎ ዛሬ የሚታወቁ [[ሲቡላውያንየሲቢሊን ንግሮችራዕዮች]] የተባሉት ሰነዶች ኦሪጂናል መሆናቸው ለምሁሮች አይመስላቸውም። ከመጀመርያ ሲቡሎች በኋላ ሌሎች ሲቡሎችሲቢሎች እንደ ተከተሉ ለንግሮቹም እንደ ጨመሩ ይታስባል።
 
በ[[መጽሐፈ ኩፋሌ]] የሴም፣ የካምና የያፌት ሚስቶች እንዲሁ ተብለው ይሰየማሉ፤
መስመር፡ 10፦
ከዚህ በላይ ሦስቱ የኖህ ልጆች ከጥቂት ዓመት በኋላ ከ[[አራራት]] ሠፈር በየአቅጣጫው ሂደው ለሰው ልጆች ሁሉ እናቶቻቸው ለሆኑት ለሚስቶቻቸው ስሞች የተባሉ 3 መንደሮች እንደ መሠረቱ ይታረካል።
 
በኋላ ዘመን የክርስቲያን ጸሓፊ [[ቅዱስ አቡሊድስ]] ([[227]] ዓ.ም. የሞቱ) በ[[ሶርያጽርዕ ታርጉም]] ዘንድ ለዚህ ተመሳሳይ የሆነ ታሪክ መዘገቡ። ነገር ግን እዚህ የሴምና የካም ሚስቶች ስሞች እንዳለዋወጡ ይመስላል። እሱ እንዲሁ፦ «የኖህ ልጆች ሚስቶች ስሞች አንዲሁ ናቸው፤ የሴም ሚስት፣ '''ናሐላጥ ማሕኑቅ'''፤ የካምም ሚስት፣ '''ዘድቃጥ ናቡ'''፣ የያፈትም ሚስት '''አራጥቃ''' ይባላሉ» ብሎ ጻፈ።
 
[[ጆን ጊል]] ([[1697 እ.ኤ.አ.|1697]]-[[1771 እ.ኤ.አ.]]) በመጽሓፍ ቅዱስ ነክ አስተያይቶቹ ስለ አንድ የ[[ዓረብ]] አፈ ታሪክ የጻፈው እንዲሁ ነው፤ «የሴም ሚስት ስም '''ዛልበጥ''' ወይም '''ዛሊጥ''' ወይም '''ሳሊት''' ሲሆን፣ የካምም ደግሞ '''ናሓላጥ''' ተባለች፣ የያፌትም ደግሞ '''አረሢሢያ''' ተባለች።
 
''[[ኪታብ አል-ማጋል]]'' የተባለው ጥንታዊ [[አረብኛ]] መጽሐፍ (ከ'[[ቄሌምንጦስ]] መጻሕፍት' መሃል)፣ በ[[ጽርዕ]] የተጻፈው መጽሐፍ [[የመዝገቦች ዋሻ]] (350 ዓ.ም. ገዳማ) እና የ[[እስክንድርያ]] ግሪክ ኦርቶዶክስ አቡነ [[ዩቲኪዮስ]] (920 ዓ.ም. ገዳማገደማ) ሁሉ ሲስማሙ የኖህን ሚስት '''ሃይኬል''' ይሏታል፤ እርስዋም የናሙስ ልጅ፣ ናሙስም የሄኖክ ሴት ልጅ፣ ይህም ሄኖክ የማቱሳላ ወንድም እንደ ነበሩ ይላሉ። ''ኪታብ አል-ማጋል'' ደግሞ የሴም ሚስት የናሲህ ልጅ '''ልያ''' ብሎ ይሰይማታል።
 
[[የሳላሚስ አጲፋንዮስ]] የጻፈው ''[[ፓናሪዮስፓናሪዮን]]'' ደግሞ የኖህ ሚስት '''ባርጤኖስ''' ይላታል። በ5ኛ ክፍለ ዘመን አካባቢ በ[[ግዕዝ]] የተሠራው ''[[መጽሐፈ አዳምና ሕይዋን]]'' ግን የኖህ ሚስት '''ሃይካል''' ሲጠራት ይቺ የአባራዝ ልጅ፣ አባራዝም የ[[ሄኖስ]] ልጆች ሴት ልጅ ናት ይላል። አንዳንድ ጸሐፊ ስለዚህ የአጲፋንዮስ 'ባርጤኖስ' ማለት ከእብራይስጥ 'ባጥ-ኤኖስ' መሆኑን አጠቁሟል።<ref>[http://books.google.com/books?id=G0uQfRWuU4wC&pg=PA268&lpg=PA268&dq=abaraz+enos&source=web&ots=SgeVHo6Cvw&sig=Xf4POxB51QCMhFNI2CZyQdO4GlY ''A Dictionary of Christian Biography, Literature, Sects...'' p. 268]</ref>.
 
በ'ሲቡላውያንሲቢሊን ንግሮችራዕዮች' ዘንድ፣ ከሲቡሎቹከሲቢሎቹ የአንዲቱ ስም ለ'''ዛልበጥ''' ተመሳሳይ ነበረ፤ እሷም የ«ባቢሎን ሲቡልሲቢል» '''ሳምበጥ''' ነበረች። ከጥፋት ውሃ 900 አመት በኋላ ወደ [[ግሪክ (አገር)|ግሪክ]] አገር ሄዳ የንግሮች ጽሑፍ እንደ ጀመረች ብላ ጻፈች። ከዚያ በላይ የጻፈችው ጽሁፍ ከማየ አይህ አስቀድሞ የነበሩ የቤተሠቧ ስሞች ይታርካል። እነሱም አባቷ ''ግኖስቲስ''፣ እናቷ ''ኪርኬ''፤ እህቷም ''ዒሲስ'' ናቸው። በሌሎች ጥንታዊ ምንጮች ደግሞ '''ሳባ''' የምትባል ሲቡል ኖረች።
 
በ[[15ኛ ክፍለ ዘመን]] አውሮፓዊ መነኩሴ [[አኒዮ ዳ ቪተርቦ]] ዘንድ፣ [[ከለዳዊ]]ው [[ቤሮሱስቤሮሶስ]] ([[ክ.በ.280 280ዓክልበ]] ዓመት ያህል የጻፈ) የልጆቹ ሚስቶች '''ፓንዶራ፣ ኖኤላ፣ ኖኤግላ''' የኖህም ሚስት '''ቲቴያ''' ተብለው እንደ ተሰየሙ ብለው ነበር። ነገር ግን ይህ አኒዮ ዛሬ አታላይ ጸሐፊ እንደ ነበር ይታመናል[http://books.google.com/books?id=FyskAAAAMAAJ&pg=PA207&lpg=PA207&dq=berosus+pandora+noela&source=web&ots=yq6RpckzkN&sig=l-bE36p_2w521y1-H3GNyqtgYgs#PPA207,M1] ።
 
በ[[አይርላንድ]] አፈ ታሪክ ስለ ሦስቱ ልጆችና ስለ ሚስቶቻቸው የሚተረተው ብዙ አለ። በዚሁ ምንጭ ሚስቶቹ '''ኦላ፣ ኦሊቫ፣ ኦሊቫኒ''' ይባላሉ። እነኚህም ስሞች የተወሰዱ [[ኮዴክስ ጁኒየስ]] ከተባለው ጥንታዊ ([[700]] ዓ.ም.) [[እንግሊዝ]] [[ብራና ጥቅል]] ይመስላል። ይኸው ጽሕፈት እንደ ረጅም [[ግጥም]] ሆኖ በገጣሚው በ[[ካድሞን]] እንደተጻፈ ይታሥባል። እዚህ ደግሞ የኖህ ሚስት '''ፔርኮባ''' ትባላለች።
 
የ[[ሀንጋሪ]] አፈ ታሪክ ደግሞ ስለ ያፌትና '''ኤነሕ''' ስለ ተባለችው ስለ ሚስቱ አንዳንድ ተረት አለበት። ይህ መረጃ የሚገኘው የ[[አንጥያኮስአንጾኪያ]] [[ጳጳስ]] [[ሲጊልበርት]] ከተጻፉት ዜና መዋዕል እንደ ሆነ ይባላል።
 
በደቡብ [[ኢራቅ]] በሚኖሩት በጥንታዊ [[ማንዳያውያን]] ሐይማኖት ተከታዮች መጻሕፍት ዘንድ፤ የኖህ ሚስት '''ኑራይታ''' ወይም '''አኑራይጣ''' ተባለች።