ከ«የማርቆስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
No edit summary |
||
መስመር፡ 13፦
=='''ምዕራፍ ፩'''==
1፤የእግዚአብሔር፡ልጅ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ወንጌል፡መዠመሪያ።
2-3፤እንሆ፥መንገድኽን፡የሚጠርግ፡መልክተኛዬን፡በፊትኽ፡እልካለኹ፡የጌታን፡መንገድ፡
አዘጋጁ፡ጥርጊያውንም፡አቅኑ፡እያለ፡በምድረ፡በዳ፡የሚጮኽ፡ሰው፡ድምፅ፡ተብሎ፡
በነቢዩ፡በ[[ኢሳይያስ]]፡እንደ፡ተጻፈ፥
4፤ዮሐንስ፡በምድረ፡በዳ፡እያጠመቀ፡የንስሓንም፡ጥምቀት፡ለኀጢአት፡
ስርየት፡እየሰበከ፡መጣ።
5፤የይሁዳም፡አገር፡ዅሉ፡የኢየሩሳሌምም፡ሰዎች፡ዅሉ፡ወደ፡ርሱ፡ይወጡ፡ነበር፥
ኀጢአታቸውንም፡እየተናዘዙ፡በዮርዳኖስ፡ወንዝ፡ከርሱ፡ይጠመቁ፡ነበር።
6፤ዮሐንስም፡የግመል፡ጠጕር፡ለብሶ፡በወገቡ፡ጠፍር፡ይታጠቅ፡አንበጣና፡የበረሓ፡
ማርም፡ይበላ፡ነበር።
7፤ተጐንብሼ፡የጫማውን፡ጠፍር፡መፍታት፡የማይገ፟ባ፟ኝ፡
ከእኔ፡የሚበረታ፡በዃላዬ፡ይመጣል።
8፤እኔ፡በውሃ፡አጠመቅዃችኹ፡ርሱ፡ግን፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ያጠምቃችዃል፡እያለ፡
ይሰብክ፡ነበር።
9፤በዚያ፡ወራትም፡ኢየሱስ፡ከገሊላ፡ናዝሬት፡መጥቶ፡ከዮሐንስ፡በዮርዳኖስ፡ወንዝ፡ተጠመቀ።
{|
|-
Line 28 ⟶ 52:
|}
10፤ወዲያውም፡ከውሃው፡በወጣ፡ጊዜ፡ሰማያት፡ሲቀደዱ፡መንፈስም፡እንደ፡ርግብ፡ሲወርድበት፡
አየና፦የምወድኽ፡ልጄ፡አንተ፡ነኽ፥
11፤ባንተ፡ደስ፡ይለኛል፡የሚል፡ድምፅ፡ከሰማያት፡መጣ።
12፤ወዲያውም፡መንፈስ፡ወደምድረ፡በዳ፡አወጣው።
13፤በምድረ፡በዳም፡ከሰይጣን፡እየተፈተነ፡አርባ፡ቀን፡ሰነበተ፡ከአራዊትም፡ጋራ፡ነበረ፥
መላእክቱም፡አገለገሉት።
14-15፤ዮሐንስም፡ዐልፎ፡ከተሰጠ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡የእግዚአብሔርን፡መንግሥት፡ወንጌል፡
እየሰበከና፦ዘመኑ፡ተፈጸመ፡የእግዚአብሔርም፡መንግሥት፡ቀርባለች፡ንስሓ፡ግቡ፡
በወንጌልም፡እመኑ፡እያለ፡ወደ፡ገሊላ፡መጣ።
16፤በገሊላ፡ባሕርም፡አጠገብ፡ሲያልፍ፡ስምዖንን፡ወንድሙንም፡እንድርያስን፡መረባቸውን፡
ወደ፡ባሕር፡ሲጥሉ፡አየ፥ዓሣ፡አጥማጆች፡ነበሩና።
17፤ኢየሱስም፦በዃላዬ፡ኑና፡ሰዎችን፡አጥማጆች፡እንድትኾኑ፡አደርጋችዃለኹ፡አላቸው።
18፤ወዲያውም፡መረባቸውን፡ትተው፡ተከተሉት።
19፤ከዚያም፡ጥቂት፡እልፍ፡ብሎ፡የዘብዴዎስን፡ልጅ፡ያዕቆብን፡ወንድሙንም፡ዮሐንስን፡ደግሞ፡በታንኳ፡
ላይ፡መረባቸውን፡ሲያበጁ፡አየ።
20፤ወዲያውም፡ጠራቸው፡አባታቸውንም፡ዘብዴዎስን፡ከሞያተኛዎቹ፡ጋራ፡በታንኳ፡ላይ፡
ትተው፡ተከትለውት፡ኼዱ።
21፤ወደ፡ቅፍርናሖምም፡ገቡ፤ወዲያውም፡በሰንበት፡ወደ፡ምኵራብ፡ገብቶ፡አስተማረ።
22፤እንደ፡ባለሥልጣን፡ያስተምራቸው፡ነበር፡እንጂ፡እንደ፡ጻፊዎች፡አይደለምና፡በትምህርቱ፡
ተገረሙ።
23፤በዚያን፡ጊዜም፡በምኵራባቸው፡ርኩስ፡መንፈስ፡ያለው፡ሰው፡ነበረ፤
24፤ርሱም፦የናዝሬቱ፡ኢየሱስ፡ሆይ፥ከአንተ፡ጋራ፡ምን፡አለን፧ልታጠፋን፡መጣኽን፧ማን፡እንደ፡
ኾንኽ፡ዐውቄያለኹ፥የእግዚአብሔር፡ቅዱሱ፡ብሎ፡ጮኸ።
25፤ኢየሱስም፦ዝም፡በል፡ከርሱም፡ውጣ፡ብሎ፡ገሠጸው።
26፤ርኩሱም፡መንፈስ፡አንፈራገጠውና፡በታላቅ፡ድምፅ፡ጮኾ፡ከርሱ፡ወጣ።
27፤ዅሉም፦ይህ፡ምንድር፡ነው፧በሥልጣን፡ርኩሳን፡መናፍስትን፡ያዛ፟ል፤እነርሱም፡
ይታዘዙለታልና፥ይህ፡ዐዲስ፡ትምህርት፡ምንድር፡ነው፧ብለው፡እስኪጠያየቁ፡ድረስ፡አደነቁ።
28፤ዝናውም፡ወዲያው፡በየስፍራው፡ወደገሊላ፡ዙሪያ፡ዅሉ፡ወጣ።
29፤ወዲያውም፡ከምኵራብ፡ወጥቶ፡ከያዕቆብና፡ከዮሐንስ፡ጋራ፡ወደስምዖንና፡ወደእንድርያስ፡ቤት፡ገባ።
30፤የስምዖንም፡ዐማት፡በንዳድ፡ታማ፡ተኝታ፡ነበር፥ስለ፡ርሷም፡ወዲያው፡ነገሩት።
31፤ቀርቦም፡እጇን፡ይዞ፡አስነሣት፡ንዳዱም፡ወዲያው፡ለቀቃትና፡አገለገለቻቸው።
32፤ፀሓይም፡ገብቶ፡በመሸ፡ጊዜ፥የታመሙትንና፡አጋንንት፡ያደረባቸውን፡ዅሉ፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፤
33፤ከተማዪቱም፡ዅላ፡በደጅ፡ተሰብስባ፡ነበር።
34፤በልዩ፡ልዩ፡ደዌም፡የታመሙትን፡ብዙዎችን፡ፈወሰ፥ብዙዎችንም፡አጋንንት፡አወጣ፥
አጋንንትም፡ክርስቶስ፡መኾኑን፡ዐውቀው፡ነበርና፥ሊናገሩ፡አልፈቀደላቸውም።
35፤ማለዳም፡ተነሥቶ፡ገና፡ሌሊት፡ሳለ፡ወጣ፡ወደ፡ምድረ፡በዳም፡ኼዶ፡በዚያ፡ጸለየ።
36፤ስምዖንና፡ከርሱ፡ጋራ፡የነበሩትም፡ገሥግሠው፡ተከተሉት፥
37፤ባገኙትም፡ጊዜ፦ዅሉ፡ይፈልጉኻል፡አሉት።
38፤ርሱም፦በዚያ፡ደግሞ፡ልሰብክ፡ወደ፡ሌላ፡ስፍራ፡በቅርብ፡ወዳሉ፡መንደሮች፡እንኺድ፡ስለዚህ፡ወጥቻለኹና፡አላቸው።
39፤በምኵራባቸውም፡እየሰበከ፡አጋንንትንም፡እያወጣ፡ወደ፡ገሊላ፡ዅሉ፡መጣ።
40፤ለምጻምም፡ወደ፡ርሱ፡መጥቶ፡ተንበረከከና፦ብትወድስ፡ልታነጻኝ፡ትችላለኽ፡ብሎ፡ለመነው።
41፤ኢየሱስም፡ዐዘነለት፡እጁንም፡ዘርግቶ፡ዳሰሰውና፦እወዳ፟ለኹ፤ንጻ፡አለው።
42፤በተናገረም፡ጊዜ፡ለምጹ፡ወዲያው፡ለቀቀውና፡ነጻ።
43፤በብርቱም፡ተናግሮ፡ወዲያው፡አወጣው፤
44፤ለማንም፡አንዳች፡እንዳትናገር፡ተጠንቀቅ፥ነገር፡ግን፥ኼደኽ፡ራስኽን፡ለካህን፡አሳይ፡ለእነርሱም፡ምስክር፡እንዲኾን፡
ስለ፡መንጻትኽ፡ሙሴ፡ያዘዘውን፡አቅርብ፡አለው።
45፤ርሱ፡ግን፡ሲወጣ፡ብዙ፡ሊሰብክና፡ነገሩን፡ሊያወራ፡ዠመረ፥ስለዚህም፡ኢየሱስ፡ተገልጦ፡ወደ፡ከተማ፡መግባት፡ወደ፡
ፊት፡ተሳነው፥ነገር፡ግን፥በውጭ፡በምድረ፡በዳ፡ይኖር፡ነበር፤ከየስፍራውም፡ወደ፡ርሱ፡ይመጡ፡ነበር።
{|
|-
|