ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,213፦
39፤እላችዃለኹና፥በጌታ፡ስም፡የሚመጣ፡የተባረከ፡ነው፡እስክትሉ፡ድረስ፡ከእንግዲህ፡ወዲህ፡አታዩኝም።
== '''ምዕራፍ ፳፬''' ==
1፤ኢየሱስም፡ከመቅደስ፡ወጥቶ፡ኼደ፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡የመቅደሱን፡ግንቦች፡ሊያሳዩት፡ቀረቡ።
2፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፦ይህን፡ዅሉ፡ታያላችኹን፧እውነት፡እላችዃለኹ፥ድንጋይ፡በድንጋይ፡ላይ፡ሳይፈርስ፡
በዚህ፡አይቀርም፡አላቸው።
3፤ርሱም፡በደብረ፡ዘይት፡ተቀምጦ፡ሳለ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፡ለብቻቸው፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦ንገረን፥ይህ፡
መቼ፡ይኾናል፧የመምጣትኽና፡የዓለም፡መጨረሻ፡ምልክቱስ፡ምንድር፡ነው፧አሉት።
4፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ማንም፡እንዳያስታችኹ፡ተጠንቀቁ።
5፤ብዙዎች፦እኔ፡ክርስቶስ፡ነኝ፡እያሉ፡በስሜ፡ይመጣሉና፤ብዙዎችንም፡ያስታሉ።
6፤ጦርንም፡የጦርንም፡ወሬ፡ትሰሙ፡ዘንድ፡አላችኹ፤ይህ፡ሊኾን፡ግድ፡ነውና፥ተጠበቁ፥አትደንግጡ፤ዳሩ፡
ግን፡መጨረሻው፡ገና፡ነው።
7፤ሕዝብ፡በሕዝብ፡ላይ፡መንግሥትም፡በመንግሥት፡ላይ፡ይነሣልና፥ራብም፡ቸነፈርም፡የምድርም፡መናወጥ፡
በልዩ፡ልዩ፡ስፍራ፡ይኾናል፤
8፤እነዚህም፡ዅሉ፡የምጥ፡ጣር፡መዠመሪያ፡ናቸው።
9፤በዚያን፡ጊዜ፡ለመከራ፡አሳልፈው፡ይሰጧችዃል፡ይገድሏችኹማል፥ስለ፡ስሜም፡በአሕዛብ፡ዅሉ፡
የተጠላችኹ፡ትኾናላችኹ።
10፤በዚያን፡ጊዜም፡ብዙዎች፡ይሰናከላሉ፡ርስ፡በርሳቸውም፡አሳልፈው፡ይሰጣጣሉ፥ርስ፡በርሳቸውም፡ይጣላሉ፤
11፤ብዙ፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያትም፡ይነሣሉ፡ብዙዎችንም፡ያስታሉ፤
12፤ከዐመፃም፡ብዛት፡የተነሣ፡የብዙ፡ሰዎች፡ፍቅር፡ትቀዘቅዛለች።
13፤እስከ፡መጨረሻ፡የሚጸና፡ግን፡ርሱ፡ይድናል።
14፤ለአሕዛብም፡ዅሉ፡ምስክር፡እንዲኾን፡ይህ፡የመንግሥት፡ወንጌል፡በዓለም፡ዅሉ፡ይሰበካል፥በዚያን፡
ጊዜም፡መጨረሻው፡ይመጣል።
15፤እንግዲህ፡በነቢዩ፡በዳንኤል፡የተባለውን፡የጥፋትን፡ርኵሰት፡በተቀደሰችው፡ስፍራ፡ቆሞ፡ስታዩ፥አንባቢው፡
ያስተውል፥
16፤በዚያን፡ጊዜ፡በይሁዳ፡ያሉት፡ወደ፡ተራራዎች፡ይሽሹ፥
17፤በሰገነትም፡ያለ፡በቤቱ፡ያለውን፡ሊወስድ፡አይውረድ፥
18፤በዕርሻም፡ያለ፡ልብሱን፡ይወስድ፡ዘንድ፡ወደ፡ዃላው፡አይመለስ።
19፤በዚያችም፡ወራት፡ለርጕዞችና፡ለሚያጠቡ፡ወዮላቸው።
20፤ነገር፡ግን፥ሽሽታችኹ፡በክረምት፡ወይም፡በሰንበት፡እንዳይኾን፡ጸልዩ፤
21፤በዚያን፡ጊዜ፡ከዓለም፡መዠመሪያ፡ዠምሮ፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡ያልኾነ፡እንግዲህም፡ከቶ፡የማይኾን፡
ታላቅ፡መከራ፡ይኾናልና።
22፤እነዚያ፡ቀኖችስ፡ባያጥሩ፡ሥጋ፡የለበሰ፡ዅሉ፡ባልዳነም፡ነበር፤ነገር፡ግን፥እነዚያ፡ቀኖች፡
ስለተመረጡት፡ሰዎች፡ያጥራሉ።
23፤በዚያን፡ጊዜ፡ማንም፦እንሆ፥ክርስቶስ፡ከዚህ፡አለ፡ወይም፦ከዚያ፡አለ፡ቢላችኹ፡አትመኑ፤
24፤ሐሰተኛዎች፡ክርስቶሶችና፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያት፡ይነሣሉና፥ቢቻላቸውስ፡የተመረጡትን፡እንኳ፡እስኪያስቱ፡
ድረስ፡ታላላቅ፡ምልክትና፡ድንቅ፡ያሳያሉ።
25፤እንሆ፥አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ።
26፤እንግዲህ፦እንሆ፥በበረሓ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትውጡ፤እንሆ፥በዕልፍኝ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትመኑ፤
27፤መብረቅ፡ከምሥራቅ፡ወጥቶ፡እስከ፡ምዕራብ፡እንደሚታይ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና፤
28፤በድን፡ወዳለበት፡በዚያ፡አሞራዎች፡ይሰበሰባሉ።
29፤ከዚያች፡ወራትም፡መከራ፡በዃላ፡ወዲያው፡ፀሓይ፡ይጨልማል፥ጨረቃም፡ብርሃኗን፡
አትሰጥም፥ከዋክብትም፡ከሰማይ፡ይወድቃሉ፥
30፤የሰማያትም፡ኀይላት፡ይናወጣሉ።በዚያን፡ጊዜም፡የሰው፡ልጅ፡ምልክት፡በሰማይ፡ይታያል፥በዚያን፡
ጊዜም፡የምድር፡ወገኖች፡ዅሉ፡ዋይ፡ዋይ፡ይላሉ፥የሰው፡ልጅንም፡በኀይልና፡በብዙ፡ክብር፡በሰማይ፡ደመና፡
ሲመጣ፡ያዩታል፤
31፤መላእክቱንም፡ከታላቅ፡መለከት፡ድምፅ፡ጋራ፡ይልካቸዋል፥ከሰማያትም፡ዳርቻ፡እስከ፡ዳርቻው፡ከአራቱ፡
ነፋሳት፡ለርሱ፡የተመረጡትን፡ይሰበስባሉ።
32፤ምሳሌውንም፡ከበለስ፡ተማሩ፤ጫፏ፡ሲለሰልስ፡ቅጠሏም፡ሲያቈጠቍጥ፥ያን፡ጊዜ፡በጋ፡እንደ፡ቀረበ፡
ታውቃላችኹ፤
33፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡ይህን፡ዅሉ፡ስታዩ፡በደጅ፡እንደ፡ቀረበ፡ዕወቁ።
34፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡እስኪኾን፡ድረስ፡ይህ፡ትውልድ፡አያልፍም።
35፤ሰማይና፡ምድር፡ያልፋሉ፥ቃሌ፡ግን፡አያልፍም።
36፤ስለዚያች፡ቀንና፡ስለዚያች፡ሰዓት፡ግን፡ከአባት፡ብቻ፡በቀር፡የሰማይ፡መላእክትም፡ቢኾኑ፡ልጅም፡
ቢኾን፡የሚያውቅ፡የለም።
37፤የኖኅ፡ዘመን፡እንደ፡ነበረ፡የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና።
38፤በዚያች፡ወራት፡ከጥፋት፡ውሃ፡በፊት፥ኖኅ፡ወደ፡መርከብ፡እስከገባበት፡ቀን፡ድረስ፥ሲበሉና፡ሲጠጡ፡
ሲያገቡና፡ሲጋቡም፡እንደ፡ነበሩ፥
39፤የጥፋት፡ውሃም፡መጥቶ፡ዅሉን፡እስከወሰደ፡ድረስ፡እንዳላወቁ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡ደግሞ፡እንዲሁ፡
ይኾናል።
40፤በዚያን፡ጊዜ፡ኹለት፡ሰዎች፡በዕርሻ፡ይኾናሉ፤አንዱ፡ይወሰዳል፡አንዱም፡ይቀራል፤
41፤ኹለት፡ሴቶች፡በወፍጮ፡ይፈጫሉ፤አንዲቱ፡ትወሰዳለች፡አንዲቱም፡ትቀራለች።
42፤ጌታችኹ፡በምን፡ሰዓት፡እንዲመጣ፡አታውቁምና፡እንግዲህ፡ንቁ።
43፤ያን፡ግን፡ዕወቁ፤ባለቤት፡ከሌሊቱ፡በየትኛው፡ክፍል፡ሌባ፡እንዲመጣ፡ቢያውቅ፡ኖሮ፥በነቃ፡ቤቱም፡
ሊቈፈር፡ባልተወም፡ነበር።
44፤ስለዚህ፥እናንተ፡ደግሞ፡ተዘጋጅታችኹ፡ኑሩ፥የሰው፡ልጅ፡በማታስቡበት፡ሰዓት፡ይመጣልና።
45፤እንኪያስ፡ምግባቸውን፡በጊዜው፡ይሰጣቸው፡ዘንድ፡ጌታው፡በቤተ፡ሰዎች፡ላይ፡የሾመው፡ታማኝና፡
ልባም፡ባሪያ፡ማን፡ነው፧
46፤ጌታው፡መጥቶ፡እንዲህ፡ሲያደርግ፡የሚያገኘው፡ያ፡ባሪያ፡ብፁዕ፡ነው፤
47፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ባለው፡ዅሉ፡ላይ፡ይሾመዋል።
48፤ያ፡ክፉ፡ባሪያ፡ግን፦ጌታዬ፡እስኪመጣ፡ይዘገያል፡ብሎ፡በልቡ፡ቢያስብ፥
49፤ባልንጀራዎቹን፡ባሪያዎች፡ሊመታ፡ቢዠምር፥ከሰካሮችም፡ጋራ፡ቢበላና፡ቢጠጣ፥
50፤የዚያ፡ባሪያ፡ጌታ፡ባልጠበቃት፡ቀን፡ባላወቃትም፡ሰዓት፡ይመጣል፥
51፤ከኹለትም፡ይሰነጥቀዋል፥ዕድሉንም፡ከግብዞች፡ጋራ፡ያደርግበታል፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡
ይኾናል።
== '''ምዕራፍ ፳፭''' ==