ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,093፦
46፤ሊይዙትም፡ሲፈልጉት፡ሳሉ፡ሕዝቡ፡እንደ፡ነቢይ፡ስላዩት፡ፈሯቸው።
== '''ምዕራፍ ፳፪''' ==
1፤ኢየሱስም፡መለሰ፡ደግሞም፡በምሳሌ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አለ፦
2፤መንግሥተ፡ሰማያት፡ለልጁ፡ሰርግ፡ያደረገ፡ንጉሥን፡ትመስላለች።
3፤የታደሙትንም፡ወደ፡ሰርጉ፡ይጠሩ፡ዘንድ፡ባሮቹን፡ላከ፡ሊመጡም፡አልወደዱም።
4፤ደግሞ፡ሌላዎችን፡ባሪያዎች፡ልኮ፦የታደሙትን፦እንሆ፥ድግሴን፡አዘጋጀኹ፥ኰርማዎቼና፡የሰቡት፡
ከብቶቼ፡ታርደዋል፥ዅሉም፡ተዘጋጅቷል፤ወደ፡ሰርጉ፡ኑ፡በሏቸው፡አለ።
5፤እነርሱ፡ግን፡ቸል፡ብለው፡አንዱ፡ወደ፡ዕርሻው፥ሌላውም፡ወደ፡ንግዱ፡ኼደ፤
6፤የቀሩትም፡ባሮቹን፡ይዘው፡አንገላቷቸው፡ገደሏቸውም።
7፤ንጉሡም፡ተቈጣ፥ጭፍራዎቹንም፡ልኮ፡እነዚያን፡ገዳዮች፡አጠፋ፤ከተማቸውንም፡አቃጠለ።
8፤በዚያን፡ጊዜ፡ባሮቹን፦ሰርጉስ፡ተዘጋጅቷል፥ነገር፡ግን፥የታደሙት፡የማይገ፟ባ፟ቸው፡ኾኑ፤
9፤እንግዲህ፡ወደመንገድ፡መተላለፊያ፡ኼዳችኹ፡ያገኛችኹትን፡ዅሉ፡ወደ፡ሰርጉ፡ጥሩ፡አለ።
10፤እነዚያም፡ባሪያዎች፡ወደ፡መንገድ፡ወጥተው፡ያገኙትን፡ዅሉ፡ክፉዎችንም፡በጎዎችንም፡
ሰበሰቡ፤የሰርጉንም፡ቤት፡ተቀማጮች፡ሞሉት።
11፤ንጉሡም፡የተቀመጡትን፡ለማየት፡በገባ፡ጊዜ፡በዚያ፡የሰርግ፡ልብስ፡ያለበሰ፡አንድ፡ሰው፡አየና፦ወዳጄ፡
ሆይ፥
12፤የሰርግ፡ልብስ፡ሳትለብስ፡እንዴት፡ወደዚህ፡ገባኽ፧አለው፡ርሱም፡ዝም፡አለ።
13፤በዚያን፡ጊዜ፡ንጉሡ፡አገልጋዮቹን፦እጁንና፡እግሩን፡አስራችኹ፡በውጭ፡ወዳለው፡ጨለማ፡
አውጡት፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይኾናል፡አለ።
14፤የተጠሩ፡ብዙዎች፥የተመረጡ፡ግን፡ጥቂቶች፡ናቸውና።
15፤ስለዚህ፥ፈሪሳውያን፡ኼዱና፥እንዴት፡አድርገው፡በነገር፡እንዲያጠምዱት፡ተማከሩ።
16፤ደቀ፡መዛሙርታቸውንም፡ከሄሮድስ፡ወገን፡ጋራ፡ላኩበት፥እነርሱም፦መምህር፡ሆይ፥እውነተኛ፡እንደ፡
ኾንኽ፡በእውነትም፡የእግዚአብሔርን፡መንገድ፡እንድታስተምር፡እናውቃለን፥ለማንምም፡አታደላም፥የሰውን፡
ፊት፡አትመለከትምና፤
17፤እንግዲህ፡ምን፡ይመስልኻል፧ንገረን፡ለቄሳር፡ግብር፡መስጠት፡ተፈቅዷልን፡ወይስ፡አልተፈቀደም፧አሉት።
18፤ኢየሱስም፡ክፋታቸውን፡ዐውቆ፦እናንተ፡ግብዞች፥ስለ፡ምን፡ትፈትኑኛላችኹ፧
19፤የግብሩን፡ብር፡አሳዩኝ፡አለ።እነርሱም፡ዲናር፡አመጡለት።
20፤ርሱም፦ይህች፡መልክ፡ጽሕፈቲቱስ፡የማን፡ናት፧አላቸው።
21፤የቄሳር፡ነው፡አሉት።በዚያን፡ጊዜ፦እንኪያስ፡የቄሳርን፡ለቄሳር፡የእግዚአብሔርንም፡ለእግዚአብሔር፡
አስረክቡ፡አላቸው።
22፤ይህንም፡ሰምተው፡ተደነቁ፥ትተውትም፡ኼዱ።
23፤በዚያን፡ቀን፦ትንሣኤ፡ሙታን፡የለም፡የሚሉ፡ሰዱቃውያን፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡ፥
24፤እንዲህም፡ብለው፡ጠየቁት፦መምህር፡ሆይ፥ሙሴ፡አንድ፡ሰው፡ልጅ፡ሳይወልድ፡ሲሞት፡ወንድሙ፡
ሚስቱን፡አግብቶ፡ለወንድሙ፡ዘር፡ይተካ፡አለ።
25፤ሰባት፡ወንድማማች፡በእኛ፡ዘንድ፡ነበሩ፤ፊተኛውም፡ሚስት፡አግብቶ፡ሞተ፥ዘርም፡ስለሌለው፡ሚስቱን፡
ለወንድሙ፡ተወለት፤
26፤እንዲሁ፡ደግሞ፡ኹለተኛው፡ሦስተኛውም፥እስከ፡ሰባተኛው፡ድረስ።
27፤ከዅሉም፡በዃላ፡ሴቲቱ፡ሞተች።
28፤ዅሉ፡አግብተዋታልና፥በትንሣኤ፡ቀንስ፥ከሰባቱ፡ለማናቸው፡ሚስት፡ትኾናለች፧
29፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦መጻሕፍትንና፡የእግዚአብሔርን፡ኀይል፡አታውቁምና፡ትስታላችኹ።
30፤በትንሣኤስ፡እንደእግዚአብሔር፡መላእክት፡በሰማይ፡ይኾናሉ፡እንጂ፡አያገቡም፡አይጋቡምም።
31-32፤ስለ፡ትንሣኤ፡ሙታን፡ግን፦እኔ፡የአብርሃም፡አምላክ፥የይሥሐቅም፡አምላክ፡የያዕቆብም፡አምላክ፡
ነኝ፡የሚል፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ወደ፡እናንተ፡የተባለውን፡አላነበባችኹምን፧የሕያዋን፡አምላክ፡ነው፡
እንጂ፡የሙታን፡አይደለም።
33፤ሕዝቡም፡ይህን፡ሰምተው፡በትምህርቱ፡ተገረሙ።
34፤ፈሪሳውያንም፡ሰዱቃውያንን፡ዝም፡እንዳሠኛቸው፡በሰሙ፡ጊዜ፡ዐብረው፡ተሰበሰቡ።
35፤ከነርሱም፡አንድ፡ሕግ፡ዐዋቂ፡ሊፈትነው።
36፤መምህር፡ሆይ፥ከሕግ፡ማናቸዪቱ፡ትእዛዝ፡ታላቅ፡ናት፧ብሎ፡ጠየቀው።
37፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አለው፦ጌታ፡አምላክኽን፡በፍጹም፡ልብኽ፡በፍጹም፡ነፍስኽም፡በፍጹም፡ዐሳብኽም፡
ውደድ።
38፤ታላቂቱና፡ፊተኛዪቱ፡ትእዛዝ፡ይህች፡ናት።
39፤ኹለተኛዪቱም፡ይህችን፡ትመስላለች፥ርሷም፦ባልንጀራኽን፡እንደ፡ነፍስኽ፡ውደድ፡የምትለው፡ናት።
40፤በእነዚህ፡በኹለቱ፡ትእዛዛት፡ሕጉም፡ዅሉ፡ነቢያትም፡ተሰቅለዋል።
41-42፤ፈሪሳውያንም፡ተሰብስበው፡ሳሉ፥ኢየሱስ፦ስለ፡ክርስቶስ፡ምን፡ይመስላችዃል፧የማንስ፡ልጅ፡
ነው፧ብሎ፡ጠየቃቸው፦የዳዊት፡ልጅ፡ነው፡አሉት።
43-44፤ርሱም፦እንኪያስ፡ዳዊት፦ጌታ፡ጌታዬን፦ጠላቶችኽን፡የእግርኽ፡መረገጫ፡እስካደርግልኽ፡ድረስ፡
በቀኜ፡ተቀመጥ፡አለው፡ሲል፡እንዴት፡በመንፈስ፡ጌታ፡ብሎ፡ይጠራዋል፧
45፤ዳዊትስ፡ጌታ፡ብሎ፡ከጠራው፥እንዴት፡ልጁ፡ይኾናል፧አላቸው።
46፤አንድም፡ቃል፡ስንኳ፡ይመልስለት፡ዘንድ፡የተቻለው፡የለም፥ከዚያ፡ቀንም፡ዠምሮ፡ወደ፡ፊት፡ማንም፡ሊጠይቀው፡አልደፈረም።
== '''ምዕራፍ ፳፫''' ==