ከ«ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 5፦
 
== የወንጌል ዋና መልእክት ምንድነው? ==
የወንጌል አንኳር መልዕክት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የኃጢአት ሥርየት ነው። የድኅነት ሥራ በክርስቶስ ተፈፅሟል የአዋጁ ዋና መልዕክት ነው (ሐዋ.2፡38፣ 5፡31፣ 10፡43፣ 13፡38፣ 26፡18) ። የድኅነት ስራ በክርስቶስ ኢየሱስ ስለተከናወነ፣ ሰዎች በእርሱ እንዲያምኑ እና የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ የሚነገር የምስራች ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደተናገረው ወንጌል በመስቀል ላይ የተከናወነውን አስደናቂ የድኅነት ስራ የማወጅ ተግባር ነው፣ “መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ..” (1ቆሮ.15፡1-4)። የክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ የወንጌል ማዕከል ነው። ወንጌል ለፍጥረት ሁሉ የሚታወጅ የመስቀሉ የማዳን ሥራ ነው፣ “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው…” (1ኛ.ጢሞ.1፡15)። ወንጌል ሰዎች ከኃጢአታቸው ንስሃ በመግባት የበደላቸውን ስርየት እንዲቀበሉ ይናገራል፣ “..በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል” (ሉቃ.24፡47) ።
 
== በወንጌል የተገኘው ደኅንነት ==