ከ«ጋኔን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
የ197.156.77.127ን ለውጦች ወደ MedebBot እትም መለሰ።
መስመር፡ 1፦
'''ጋኔን''' (ነጠላ) ወይንም '''አጋንንት''' (ብዙ ቁጥር) የ[[እርኩስ መንፈስ]] አይነት ሲሆን ከ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] ተመዘው በተስፋፉ ጽሑፎች ላይ የዚህ መንፈስ ታሪክ/አፈ-ታሪክ ተጽፎ ይገኛል። ለምሳሌ [[ቀኖናዊ]] ባልሆኑት ''[[ስነ ፍጥረት]]'' እና ''[[ሰይፈ ስላሴ]]'' በተባሉ የግዕዝ መጻሕፍት።
 
አሁንም ብዙው ህብረተሰብ እንዲህ ያስባል። በ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] ስለሚጠቀሱ፣ እስካሁን ድረስ በዓለም ዙሪያ ያሉ [[አብያተ ክርስቲያናት]] ትምህርት እንዲህ ይመስላል። አጋንንት የሳይንስ እውቀት ባላቸውም ሆነ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ዘንድ እጅግ ከፍተኛ ፍርሃቻን የሚፈጥር አስተሳሰብ ነው። ነገር ግን የአጋንንት ታሪክ የሚመነጨው የ[[ሳይንስ]] አስተሳሰብ ባልተስፋፋበትና ስለ[[ቫይረስ]]ም ሆነ [[ጀርም]] በማይታወቅበት ዘመን ሲሆን ዘመናዊው የሳይንስ አስተሳሰብ ከዚህ ይለያል፣ እንደሚከተለው ይላል፦ ዋና ዓላማውም የበሽታዎችን አመጣጥ በሚያሳምን መልኩ ለመረዳት እና ለመተንበይ ነበር። ይሄ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው ያልተማረ ህብረተሰብ የሚሰራበት የነበር ነው። ስለሆነም [[ሆድ ቁርጠት]]፣ [[ጉስምት]]፣ [[ብድብድ]] ወዘተ በአጋንንት ምክንያት የሚመጡ ተደርገው ይታሰቡ ነበር።
ስለሆነም [[ሆድ ቁርጠት]]፣ [[ጉስምት]]፣ [[ብድብድ]] ያመጣሉ።
 
== የተለምዶ የአጋንንት አመጣጥ ታሪክ ==
እንደ ''ሰይፈ ስላሴ'' ታሪክ፣ በሰማይ ቤት 100 የመላዕክት ነገዶች ነበሩ። ከለታት አንድ ቀን እግዚአብሔር በሌለበት፣ [[ሰባልስዮስ]] ወይንም [[ሰይፈ ስላሴ]] የተሰኘ የመላዕክት አለቃ እኔ ሁሉን ፈጠርኩ አለ። ከ100ዎቹ ነግዶች አንደኛው ወገን ይህን የሰባልስዮስን ቃል አመነ። ይሄው ቡድን ወደ እሳት ተጣለ። ከሳት ከወጣም በኋላ የሰይጣን አገልጋይ ሆነ፡፡ የነገዱ አባላቶችም መጠሪያ ስማቸውም አጋንንት ሆነ።
 
እንደዚሁ አፈ ታሪክ 99 የመላዕክት ነገዶች ስለቀሩ እግዚአብሔር 100ውን ለመሙላት [[አዳም]]ን ፈጠረ፡፡ ሆኖም አዳም ከ[[ጭቃ]] ስለተሰራ እና [[ሰይጣን]] ደግሞ ከ[[አየር]] እና [[ብርሃን]] ስለተሰራ፣ ሰይጣን ለሰው ልጅ ክብር መስጠት እምቢ አለ፣ ስለዚህም በሁለቱ መካከል የማያቋርጥ ጠብ አለ።
 
=== የጋኔን በሽታና ባህላዊውን መድሃኒቱ ===
 
ከላይ እንደተጠቀሰው አብዛኛው በሽታ በአጋንንት ምክንያት የሚመጡ እንደንበር በብዙዎች ይታመን ነበር። ስለሆነም አንድ ግለሰብ በሽታ ሲይዘው እርሱን ለማዳን አንዱ አማራጭ አጋንንት የያዘውን ሰው በ[[ዛር]] መንፈስ በማስያዝ አጋንንቱን ከውስጡ ማስለቀቅ ነበር። የዛር መንፈስ ከአጋንንት ይሻላል ተብሎ ስለሚታመን። [[ፀበል]]፣ [[ቁርባን]] እና እንዲሁም የ[[እርግፍጋፎ]] እንጨት (Protea Abyssinica) ለፈውስ ይረዳሉ ተብለው ተጠቃሚነትን ያገኛሉ<ref>Reidulf Knut Molvaer: ''Socialization and social control in Ethiopia'' (1995) Page 47</ref>። ለ[[ኤድስ]] እና ሌሎች የቫይረስ እና [[ጀርም]] በሽታዎች በ[[ፀበል]] ፈውስ መፈለግ መሰረቱ ከዚህ የተዛባ ግንዛቤ ይፈውሳሉ።ይፈልቃል።
 
==በመጽሐፍ ቅዱስ==